Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, December 15, 2015

የ ህወሃት ሰዎች በ ጎንደር ጎሃ ሆቴል የጠሩት ስብሰባ ተቃውሞ ገጠመው






(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ)

‪‎የህወሓት‬ ከፍተኛ ባለስልጣናት በትናንትናው ዕለት ወደ ጎንደር ከተማ አምርተው ከዞኑ የካቢኔ አባላትና ከአንዳንድ የስርዓቱ ደጋፊ የሆኑ የከተማው ነዋሪዎች ጋር በጎሃ ሆቴል ውይይት ለማድረግ ሞክረው ጠንከር ያለ ተቃውሞና ውርደት ገጥሟቸዋል፡፡
====================================================
ከአዲስ አበባ ጎንደር የገቡት የአገዛዙ ባለስልጣናት የህወሓቱ አባይ ፀሀዬ፣ የህወሓት ተላላኪ የሆነው ብአዴን ቁንጮዎች በረከት ስምዖንና አዲሱ ለገሰ ናቸው፡፡ የክልሉ ሹም ገዱ አንዳርጋቸውም በአጃቢነት ተገኝቷል፡፡
አባይ፣ በረከትና አዲሱ በትናንትናው ዕለት የዞኑን ካቢኔ አባላትና ጥቂት የስርዓቱ ደጋፊ የሆኑ የከተማው ነዋሪዎችን በጎሃ ሆቴል ሰብስበው በጎንደር ስለሰፈነው አለመረጋጋት፣ አመፅና ጦርነት ለማነጋገር ሞክረው "ይህ ሁሉ ችግር ከደረሰና ሁኔታው ከቁጥጥር ውጭ ከሆነ በኋላ ምትመጡ እስከ ዛሬ የት ነበራችሁ? የህዝብ ቁጣ ጫፍ ደርሷል አሁን እናንተ መጣችሁ አልመጣችሁ የምትፈይዱት ቅንጣት ታክል ነገር የለም..." የሚል ምላሽ ያለበት ከወትሮው ለየት ያለና ጠንካራ ተቃውሞ ከተሰብሳቢው ተሰንዝሮባቸዋል፡፡ በተለይም በባለስልጣናቱና በካቢኔው መካከል የተፈጠረው እሰጣገባና ንትርክ ወደ ከረረ ያለመግባባት ውስጥ እንደከተታቸው ታውቋል፡፡
እነበረከትና አባይ የጎንደርን ነዋሪዎች በየክፍለ ከተማው ሰብስበው ለማነጋገር መድረክ እንዲያመቻቹላቸው የዞኑን ካቢኔ አባላት ጠይቀው የካቢኔ አባላቱ በአሁኑ የትኩሳት ወቅት ህዝብ መሰብሰብ ከአቅማቸው በላይ እንደሆነ እና ባለስልጣናቱ ራሳቸው ወርደው ያሻቸውን ማድረግ እንደሚችሉ ቁርጥ ያለ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
በመሆኑም እነ በረከትና አባይ ፀሀዬ ከፍተኛ ብስጭት ውስጥ ወድቀው የሚያደርጉት ጭንቅ ጥብብ ብሏቸው አሁንም በጎንደር ከተማ ጎሃ ሆቴል ውስጥ ይገኛሉ፡፡

No comments:

Post a Comment

wanted officials