Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Sunday, December 20, 2015

The United States Concerned By Clashes in Oromia, Ethiopia

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት
የቃል-አቀባይ ቢሮ
ምክትል ቃል-አቀባይ ማርክ ቶነር የሰጡት መግለጫ
አሜሪካ በኢትዮጵያ በኦሮሚያ ክልል የተፈጠረው ግጭት ያሳስባታል
አሜሪካ በኢትዮጵያ ሰሞኑን በኦሮሚያ ክልል ተከስቶ ለብዙ ሰላማዊ ሰልፈኞች ሞት መንስኤ የሆነው ግጭት በእጅጉ ያሳስባታል፡፡ ሰዎች ህይወታቸውን በዚህ መልኩ በማጣታቸው በጣም ያሳዝነናል፤ለሟች ቤተሰቦችም የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን ልንገልጽ እንወዳለን፡፡
የኢትዮጵያ መንግሥት ሰላማዊ ሰልፎችን እንዲፈቅድና ከሕዝቡ የሚነሱ አግባብነት ያላቸው ጥያቄዎችን በውይይት እንዲፈታ፤ ሰልፈኞችም ከሁከትና ከብጥብጥ ይልቅ ውይይቶችን ለማካሄድ ፈቃደኛ እንዲሆኑ እናሳስባለን፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት የልማት ዕቅዱ ከእንግዲህ ሕዝባዊ ምክክር ሳይደረግበት እንደማይተገበር በይፋ አሳውቋል፡፡ ይህንን መንግሥት በይፋ የገለፀዉን ቁርጠኝነት የምንደግፍ መሆኑን እየገለጽን፤ በቀጣይም አግባብነት ያላቸዉን ባለድርሻ አካላት በአፋጣኝ ሰብስቦ እንዲያወያይ እናሳስባለን፡፡

U.S. Department of State - Great Seal

The United States Concerned By Clashes in Oromia, Ethiopia


Press Statement

Mark C. Toner
Deputy Department Spokesperson
Washington, DC


The United States is deeply concerned by the recent clashes in the Oromia region of Ethiopia that reportedly have resulted in the deaths of numerous protestors. We greatly regret the deaths that have occurred and express our condolences to the families of those who have lost their lives.
We urge the government of Ethiopia to permit peaceful protest and commit to a constructive dialogue to address legitimate grievances. We also urge those protesting to refrain from violence and to be open to dialogue. The government of Ethiopia has stated publicly that the disputed development plans will not be implemented without further public consultation. We support the government of Ethiopia’s stated commitment to those consultations and urge it to convene stakeholders to engage in dialogue as soon as possible.

No comments:

Post a Comment

wanted officials