Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, December 15, 2015

‪#‎የአርበኞች‬ ግንቦት 7 ሰራዊት በዛሬው ዕለት መተማ አካባቢ በህወሓት የመከላከያ ኃይል ላይ ድንገተኛ የሽምቅ ውጊያ ጥቃት ከፍቶ ከፍተኛ ጉዳት አደረሰ፡

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ)
‪#የአርበኞች‬ ግንቦት 7 ሰራዊት በዛሬው ዕለት መተማ አካባቢ በህወሓት የመከላከያ ኃይል ላይ ድንገተኛ የሽምቅ ውጊያ ጥቃት ከፍቶ ከፍተኛ ጉዳት አደረሰ፡፡
====================================================
የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት ሰሞኑን በዋል ድባ እና በአድ-እርቃይ ተከታታይ የሽምቅ ውጊያ እንቅስቃሴዎችን አድርጎ የህወሓትን መከላከያ፣ ፌደራል ፖሊስና ሚሊሻ ኃይል በገፍ በመግደልና በማቁሰል ክፉኛ አሽመድምዶታል፡፡ 
ዘረኛውና ፋሽስቱ የህወሓት አገዛዝ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየፈፀመው ለሚገኘው ጭፍጨፋ የአፀፋ እርምጃ መተማ አካባቢ ተከማችቶ በሚገኘው ከፍተኛ ቁጥር ያለው የመከላከያ ኃይል ላይ ዛሬ ከሰዓት በኋላ መጠነ ሰፊና የተቀናጀ የሽምቅ ውጊያ ጥቃት ከፍቶ በሰው ኃይል፣ በትጥቅና ስንቅ ላይ እጅግ በጣም የከፋ ጉዳትና ኪሳራ አድርሷል፡፡
የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት በዛሬው ዕለት በህወሓት አገዛዝ ላይ በወሰደው ከባድ እርምጃ ከቀኑ 8፡00 እስከ 10፡00 ሰዓት ለሁለት ተከታታይ ሰዓታት በመተማ አካባቢ ሰፍሮ የቆየውን የመከላከያ ኃይል እያራወጠ በእሳት በትር ገርፎታል፡፡
የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት በመተማ ወረዳ በዘረኛውና ፋሽስቱ የህወሓት አገዛዝ መከላከያ ኃይል ላይ በወሰደው እርምጃ የህዝብ ወገን መሆኑን እንዳስመሰከረ የአካባቢው ነዋሪዎች በመግለፅ ላይ ናቸው፡፡

No comments:

Post a Comment

wanted officials