Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, December 10, 2015

በጎጃም ከተሞች የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሀይል ንቅናቄ በራሪ የትግል ጥሪዎችን በተነ!!

በጎጃም ከተሞች የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሀይል ንቅናቄ በራሪ የትግል ጥሪዎችን በተነ!!
ተነሱ ተነስተናል! ዝምታው ይብቃ!
የጎጃም ከተሞች በአማራ ዴሞክራሲያዊ ሀይል ንቅናቄ የትግል ጥሪ በራሪ ወረቀቶች አሸብርቀው አድረዋል። ተነሱ ተነስተናል! ዝምታው ይብቃ! በማለት በመላው ኢትዮጵያ እየተቀጣጠለ ያለውን ህዝባዊ አመጽ ተቀላቀሉ! የሚል መልክት የያዙ በራሪ ወረቀቶችን በባህርዳር፤ መራዊ፤ ዳንግላ፤ ቻግኒ፤ ደብረማርቆስ፤ ሞጣ እና ቢቸና ለህዝብ ተዳርሰዋል። የሕወሓትን የግፍ ስርዓት በአጭር ጊዜ ለማስወገድ አመጹ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ህዝብ የአጸፋ እርምጃ እንዲወስድ እና ከንቀናቄው ጎን እንዲቆም ጥሪ አቅርቧል።
...
የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሀይል ንቅናቄ ከአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ጋር ጥምረት በመፍጠር የኢትዮጵያ አገር አድን ንቅናቄን ከመሰረቱት ድርጅቶች አንዱ መሆኑ ይታወቃል።


No comments:

Post a Comment

wanted officials