Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, December 3, 2015

የባሌ መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሲቃወሙ አመሹ * በሃሮማያ ዩኒቨርስቲ የፌደራል ፖሊስ የፈጸመውን ግድያ አወገዙ







ፎቶ ከፋይል

(ዘ-ሐበሻ) የአዲስ አበባን አዲሱን ማስተር ፕላን በመቃወም የተነሳው የሕዝብ ቁጣ ወደ ተለያዩ ከተሞች እየተዛመተ ሲሆን የመንግስት ሚድያዎች በበኩላቸው ምንም እንዳልተፈጠረ መረጃዎቹን በማፈን ስለ እንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ እያወሩ ይገኛሉ::

በሃሮማያ ዪኒቨርሲቲ የተማሪዎቹን ሰላማዊ ጥያቄ ፖሊስ በኃይል ለመበተን ባደረገው ጥረት ሰዎች መሞታቸውና መቁሰላቸውን ዘ-ሐበሻ ቀደም ብላ መዘገቧ የሚታወስ ሲሆን ይህን ተከትሎም በባሌ መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ አመሻሹ ላይ ተማሪዎች ቁጣቸውን መግለጻቸው ተሰምቷል::

በመደወላቡ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹ ቁጣቸውን ከገለጹ በኋላ ወደ መኝታቸው እንደሄዱ የገለጹት ምንጮቻችን በተለይ በሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ በመንግስት ኃይሎች የተወሰደውን እርምጃ ተቃውመዋል::

መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ እንደሚገኝ የሚገልጹት ምንጮች አካባቢው በፖሊስ መወረሩም ተዘግቧል::

No comments:

Post a Comment

wanted officials