Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, December 28, 2015

የአርበኞች ግንቦት 7 ከፍተኛ አመራር አቶ ኤፍሬም ማዴቦ አሜሪካ ገብተዋል

Ephrem Madeno
(ዘ-ሐበሻ) የአርበኞች ግንቦት 7 ከፍተኛ አመራር አቶ ኤፍሬም ማዴቦ የነፃነት ሠራዊቱ ወዳለበት ኤርትራ በረሃ ባለፈው ኦገስት 2015 መጀመሪያ ላይ ከወረዱ በኋላ ሰሞኑን ወደ አሜሪካ እንደመጡ የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታወቁ::
የዘ-ሐበሻ ምንጮች የአርበኞች ግንቦት 7 አመራሩ አቶ ኤፍሬም ማዴቦ ለምን ወደ አሜሪካ እንደመጡ በማጣራት ላይ ይገኛሉ::
ሕወሓት በሚመራውና በሚያዝበት ፍርድ ቤት በአንዱዓለም አራጌ የክስ መዝገብ “በሃገሪቱ የመሰረተ ልማት አውታሮች ላይ፣ በሚዲያ ተቋማትና በባለስልጣናት ላይ አደጋን ለመጣል በሚል ክስ አቶ ኤፍሬም ማዴቦ እጃቸው ከተያዘበት እለት ጀምሮ በ25 ዓመት ዕኑ እስራት እንዲታሰሩ የተፈረደባቸው ፖለቲከኛ ናቸው:: በተጨማሪም ከእነ ብርጋዴር ጄነራል ተፈራ ማሞ ክስ ጋር በዕድሜ ልክ እስራት እንደተፈረደባቸው ይታወሳል::

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/49485

No comments:

Post a Comment

wanted officials