Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Sunday, December 13, 2015

ወያኔ ሰራዊቱን መምራት ተስኖታል!!


ወያኔ ሰራዊቱን መምራት ተስኖታል!!



?

ከሰሞኑ በተደጋጋሚ እየተደረገ የሚገኘዉን ጦርነት በሐላፊነት የወሰደ አካል የለም! ትግራይ እና የጎንደር ጠረፎችን እየተሻገርና እየተመላለሰ የሚያጠቃ ብርቱ ሐይል ተከስቷል! በጎንደር ሶሮቃ፡ ሳንጃ፡ አሸሬ፡ ዳንሻ እንዲሁም መተማ በሱዳን በኩል አል ቃዳሪፍ ድንገተኛ ትቃቶች ተፈራርቀዋል! የወያኔ ሰራዊት እጅ እየሰጠና እየተማረከ ነዉ! በትግራይ በሂምሮ ፣ ከሻምቡካ እስከ ባድሜ እንዲሁም በቡርኩታ በተጨማሪ ከአዲ ቀይህ እስከ አዲ ግራት እንዲሁም ከአዲ ቋላህ በኩል ወያኔ እየተጠቃ ይገኛል።
ምንጮች እንደጠቀሱት የወያኔ ታጣቂዎች በከፍተኛ ሁኔታ በማፈግፈጋቸዉ አጥቂዉ ሐይል የወሰን መስመሮችን በብዛት ተቆናጠሯል በተለይም ጥቃቶቹ የሚሰነዘሩባቸዉ ስፍራዎች ለአየር ዉጊያ የማይመቹ በመሆናቸዉና ያልተጠበቁና ከቁጥጥር ዉጭ እየሆኑ ይገኛሉ! በጎንደር በኩል ቁልፍ ቁልፍ የሆኑ የመቆጣጠሪያ ቀጠናዎች በአጥቂዉ ሐይል ሲደመሰሱ ብዛት ያላቸዉ ቀላልና ከባድ መሳሪያውችም ተማርከዋል።
ከምንጮቻችን መካከል አንዱ እንደገለጹት በአሁኑ ወቅት ትግሬ ያልሆኑ አዋጊዎች በዝዉዉር ሰብበ እየተነሱ በምትካቸዉ ትግሬዎቹ እየተቀየሩ ሲሆን በትግሬ አዋጊዎች ብቃት ማነስና ከሰራዊቱ ጋር ያለመግባባት ምክንያት ጦሩን ማቀናጀት አልተቻለም። በተጨማሪ እራሱ ሰራዊቱ በአንድ ዘር የመመራቱ ጉዳይ የማይዋጥለት ደረጃ ላይ እየደረሰ በምምጣቱ በቡድን በቡድን ተሰባጥሮ በመከፋፈል ለመታዘዝም አስቸጋሪ ሆኗል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !

No comments:

Post a Comment

wanted officials