Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Sunday, August 28, 2016

በታላቁ የአባይ ወንዝ መነሻ በሰከላ ወረዳ ህዝብ ስልጣን ተረከበ

ከ22-12-2008 ጀምሮ በአደባባይ ላይ ባደረገዉ ትልቅ አመፅ ከዳር እስከዳር ወያኔን አንቀጠቀጠ ህዝቡ በድንጋይ የወያኔን መሳሪያ መከተ አንድነት ሃይል ነዉ በማለት በቀላል ዘዴ ወያኔን ከመሃል አድርገዉ አጣበቁት ከመሬት! እስረኞች ተፈቱ……………
በአደባባይ ከብአዴን ቢሮ ሰይጣኒዝሙ ባንዲራ ወርዶ ከእግዚያብሄር የተላከልን አባቶች የተሰዉላት ሰንደቅ በከፍታ ተዉለበለበች የወያኔ ታፔላ ሁሉም ተገነጠላ!
በዛን ሰአት ወያኔ በአስገባቸዉ ሰዉ በላ የጥይት ዶፍ በሰዉ ላይ ተከፈተ ህዝቡ ተበተነ ሁሉም በወኔ ምሽግ ያዘ! እንደገና ህዝቦ ተነሳ ”ነፃነት በነፃ አይገኝም” የሚል ሞፎክር አሰሙ! በዚ የተበሳጩት የወያኔ ቅጥረኞች ወጣቱን በጥቁር መዝገብ ላይ አሰፈሩ!
በ23-12-2008 እንደገና በጠዋቱ ተጀመረ የግሽ አባይ ምድር በ ሰንደቅ አሸበረቀ ሽንፈት በቃን አለ! የአባይ ወንዝ አጉረመረመ ሰማዬ ጠቆረ ህዝብ ስልጣን ተረከበ! በአሁኑ ሰአት በአገር ሽማግሌ እየተመራች ነዉ! ድል ለህዝብ ነዉ ትግላችን ይቀጥላል.
13942395_10205155496405616_1008799724_n

No comments:

Post a Comment

wanted officials