Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, November 24, 2016

ሌንጮ ለታና ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በስዊድን ኢትዮጵያውያንን ስብሰባ ጠሩ

  • 287
    Share
የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር አርበኛ ታጋይ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግምባር መሪ አቶ ሌንጮ ለታ በስዊድን ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን ጋር ጥምረት ከመሰረቱ በኋላ የመጀመሪያውን ሕዝባዊ ስብሰባ ሊያደርጉ መሆኑ ተሰማ::
ይህ ሕዝባዊ ስብሰባ ለጥምረቱ ገቢ የ,ሚሆን የገቢማሰባሰቢያም እንደሚደረግበት ከአዘጋጆቹ ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል::
“በስቶኮልም የሚዘጋጀው ይህ መድረክ ለመጀመሪያ ጊዜ ንቅናቄው ከህዝብ ጋር የሚገናኝበት ታሪካዊ መድረክ በመሆኑ ተጋብዘዋል።
መርሃግብሩ ላይ ከፋሽስቱ የወያኔ ስርዓት ጋር ስለተጀመረው ተጋድሎ እንዲሁም አጠቃላይ የነፃነት ትግሉን የሚመለከቱ ማብራርያዋች በስፋት ይቀርቡበታል ፣ በታዳሚዋች የሚቀርቡ ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣቸዋል።” ሲል አዘጋጅ ኮሚቴው የበተነው በራሪ ወረቀት ያስረዳል::
ሕዝባዊ ስብሰባው የሚደረግበት ቦታና ቀን:-
ቦታ Immanuelkyrkan, kungstengatan17 ( Jarlplan አጠገብ ፣ ወይም Birgeral Hotel)
Tunnalbanan Rådmansgatan
ሰዓት 14፡00 ቀን ኖቬምበር 27/2016

No comments:

Post a Comment

wanted officials