Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, November 29, 2016

የአማራ ተጋድሎ ከዚህ ወዴት? ክፍል ሁለት




1. ምን አጣን?

እስካሁን ባካሔድነው ትግል በጣም ብዙ ወንድሞቻችንና እህቶቻችንን አጥተናል። የአማራ እናቶች ዳግም ምርር ብለው አዝነዋል፤ አልቅሰዋል። ሕጻናትና ወላድ እናቶች ሳይቀሩ አማራ በመሆናቸው ብቻ ተጨፍጭፈዋል። በሺሕ የሚቆጠሩ የአማራ ልጆች በየአካባቢው በሚገኙ እስር ቤቶችና የማሰቃያ ቤቶች ታጉረው የወያኔ ቶርቸር ሰለባ እየሆኑ ነው። መተማ ውስጥ በርካታ አማሮች በጅምላ ተጨፍጭፈዋል። እንደበለጠ ንብረቱ ቸኮለ ያሉ ብሩህ አእምሮ ያላቸውና የአማራ ሕዝብ ተስፋ የሆኑ ወንድሞቻችን በአነጣጥሮ ተኳሾች ተገድለዋል። አሁንም በአማራ ክልል በየቀኑ ልጆቻችን ይገደላሉ፤ ይታሰራሉ። ከዚህም አልፎ የአማራ ተጋድሎ ያርበተበተው ወያኔ፣ በአማራና በሌሎች ሕዝቦች መካከል ግጭት ለመፍጠር ከአማራ ክልል ውጪ በሚኖሩ አማሮች ላይ መጠነ ሰፊ ዘመቻ ከፍቶ እያሰቃያቸው ይገኛል።

በአጠቃላይ በዚህ የአማራ ተጋድሎ በሺሕዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን አጥተናል፤ አሁንም ልጆቻችን በየቀኑ እየተነጠቅን ነው። አሁንም የአማራ አርሶ አደር ራሱንና ንብረቱን ለመጠበቅ ከብቶቹን ሸጦ የገዛውን መሣሪያ ለመግፈፍ ብዙ ጥረት እየተደረገና በርካታ አርሶ አደሮች በገፍ እየታሰሩና እየተሰቃዩ ነው። በእኛ በኩል ለሕዝባችን ነጻነት ሲሉ የወደቁትንና አሁንም በየማጎሪያ ቤቱ የሚሰቃዩትን ወንድሞቻችንና እህቶቻችንን ዓላማ ከግቡ ሳናደርስ እንቅልፍ እንደማይወስደን ብናውቅም፣ በመገደላቸውና የእነዚህ ዘረኞች የጥቃት ሰለባ በመሆናቸው የደረሰብን ሐዘን መራር ነው!!!

2. ምን እናድርግ?

ሀ. ወያኔ ካልወደቀ ሰላም የለንም!

ወያኔ እያለ ሰላም አናገኝም። ወያኔ ካልወደቀ ሰላም የለንም። ለእኛ ሰላም ማለት ከወያኔ ነጻ መሆን ማለት ነው። ስለሆነም ወያኔን ከሕዝባችን ጫንቃ ላይ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ አሽቀንጥረን ለመጣል ሌት ተቀን ከመታገል ውጪ ምርጫ የለንም። የወያኔና የእኛ ግንኙነት የአጥፊና ጠፊ ግንኙነት ነው። ወይ ያጠፉናል፣ ወይ እናጠፋቸውና ያወጁብንን የዘር ማጥፋት ጦርነት እንቋቋማለን። ከዚህ ውጪ ምርጫ የለም!!! መቼም ቢሆን ከወንድሞቻችንና እህቶቻችን ገዳዮች ጋር ኅብረት አይኖረንም!!!

ስለሆነም እያንዳንዱ የአማራ ልጅ ከእነዚህ ደመኞቻችን ጋር ሒሳቡን ለማወራረድ ያድባ! አምርረን እንጥላቸው! እንጸየፋቸው! ሁላችንም በምንችለው መንገድ እንታገላቸው! የወንድሞቻችን ደም ሳንመልስ እረፍት የለንምና ሁላችንም ወያኔን ለማጥፋት እንትጋ!!! ከወንድሞቹ ገዳዮች ጋር የሚተቃቀፍ ባንዳና ምንደኛ ብቻ ነው። ባንዳነት ደግሞ የአማራ ሕዝብ ዕሴት አይደለም። የወንድሞቻችን ደም ይጮሃል!!!!!

ለ. ከባንዳዎች ጋር ያለንን ሒሳብ እናወራርድ፤

የአማራ ሕዝብ ከወያኔ ዘረኛ አገዛዝ ጋር የሚያደርገውን ትግል የሚደግፉ በርካታ የብአዴን አባላት አሉ። እነዚህ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ምንም እንኳን ትግሉ የራሳቸው ትግል ቢሆንም፣ ወያኔ ሊያደርስባቸው የሚችለውን መከራ እያወቁ ከሕዝባቸው ጋር በመቆማቸው ሊመሰገኑና ክብር ሊሰጣቸው ይገባል። የእነዚህን የሕዝብ ልጆች ውለታ ሕዝባቸው እንደሚከፍላቸው አንጠራጠርም። በነበረከት ስምዖንና ከበደ ጫኔ የሚመራው የብአዴን ምንደኛ አመራር ከወያኔ የሚሰጠውን ተልዕኮ በመያዝ የሕዝብ ወገንተኝነት የሚያሳዩትን የብአዴን አመራሮች ለመመንጠር ደፋ ቀና እያለ እንደሚገኝ እናውቃለን። ሆኖም ይህ የብአዴን ምንደኛ አመራር ከሕዝቡ ጋር የተቆራረጠ ስለሆነ፣ ለጊዜው በወያኔ ጫንቃ ላይ ታዝሎ እንቡር እንቡር ቢልም በሰፊው የአማራ ሕዝብ ትግል እንክትክቱ እንደሚወጣ ጥርጥር የለንም።

በእኛ በኩል ግንባር ቀደም ጠላታችን ወያኔን እየታገልን፣ እዚያው በዚያው የዚህ ጸረ አማራ ቡደን ተላላኪ ሆነው በሕዝባችን ላይ መጠነ ሰፊ በደል የሚፈጽሙትን ምንደኞችና ባንዳዎችም መመንጠር ይኖርብናል። እነዚህ የሕዝባቸውን ጡት የሚነክሱ የለየላቸው ከሃዲዎች ከጥፋት ድርጊታቸው እንዲመለሱና የሕዝቡን ትግል እንዲቀላቀሉ እንዲመከሩ ከተደረገ በኋላ፣ የሕዝቡን ጥሪ አልሰማም ብለው በጥፋት ተግባራቸው የሚቀጥሉ ከሆነ ጠላት ናቸውና መደምሰስ ይኖርባቸዋል። እነዚህን ተመክረው አልሰማ ያሉ ባንዳዎች ሁሉም አማራ፣ ሴት ወንድ ሳይባል በሚችለው መንገድና መሣሪያ እንዲያስወግዳቸው ያስፈልጋል። ወያኔ ያለነዚህ መንገድ መሪዎች ወደመንደሮቻችን መግባት አይችልም። ስለሆነም እነዚህ የጥፋት ተባባሪዎች እንዲመከሩ፣ ተመክረው የማይሰሙ ከሆነ ደግሞ እንዲደመሰሱ ማድረግ በጣም አስፈላጊ ነው። ከእነዚህ ጸረ ሕዝቦች ጋር አብሮ መዋል፣ አብሮ መብላትና መጠጣት፣ ከእነሱ ለቅሶ መድረስም ሆኖ ሌላ ማንኛውንም ማኅበራዊ ግንኙነት መመሥረት ከጠላት ጋር መተባበር ስለሆነ ግንኙነታችንም መልክ መያዝ ይገባዋል። ጠላት መጠላት አለበት፤ ከዚያም አልፎ ጠላት ነውና እንዲወገድ ያስፈልጋል።

እነዚህ ባንዳዎች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከታወጀ ጊዜ ጀምሮ እንደገና የአማራ ልጆችን ለወያኔ አራጆች አሳልፈው ለመስጠት ደፋ ቀና እያሉ ነው። እነዚህ ከንቱዎች የወያኔ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሁሉንም ነገር የሚያረጋጋውና እነሱም ወደቀደም የምቾት ሕይወታቸው የሚመለሱ ይመስላቸዋል። ሆኖም እነዚህ የታሪክ አተላዎች ከሐቅና ከታሪክ ጋር የሚጋጭ አቋም እንደሚያራምዱ የአማራ ሕዝብ በቅርብ ጊዜ ያስገነዝባቸዋል። የእነዚህ ምንደኞች የምቾት ሕይወት ላይመለስ ተቀብሯል። ለአዲሱ ትንታግ የአማራ ትውልድ ምስጋና ይግባውና እነዚህ ወንድሞቻችንን ለጠላት አሳልፈው የሚሰጡ ምንደኞች ይመነጠራሉ፤ የእጃቸውን ያገኛሉ። በየዕለቱ ማን ምን እንደሚሠራ፣ ማን ታጋይ እንደሆነ፣ ማን የሕዝብ ወዳጅ፣ ማን ጠላት እንደሆነ በሚገባ እየተጣራ ይሰነዳል፤ ጊዜው ሲደርስ በምንደኞች ላይ የማያዳግም እርምጃ ይወሰዳል።

ሐ. ከአንድነት ኃይሉ ጋር ያለንን ሚና እንለይ፤

በእኛ በአማራ ልጆችና በአማራ ብሔርተኞች ዕይታ፣ የአማራ ሕዝብ በነብሰ ገዳዩ ወያኔ አገዛዝ ሲቀጠቀጥ የኖረው በማንነቱ፣ አማራ በመሆኑ ምክንያት ነው። ስለሆነም ሕዝባችን ከዚህ የወያኔ ጭቆናና ከታወጀበት የዘር ፍጅት ራሱን መከላከል እና ነጻነቱን ማስከበር የሚችለው እንደአማራ ሲደራጅና እንደአማራ ሲታገል ነው የሚል የማያወላውል አቋም አለን። የአንድነት ኃይል ነን የሚሉት ሰዎች ይህን አይፈልጉም። ብዙ አማሮች ሳይቀሩ፣ ሕዝባችን በማንነቱ ተደራጅቶ የተደቀነበትን አደጋ እንዳይቋቋምና ዘላቂ ጥቅሙን እንዳያስከብር አማራ ከተደራጀ ኢትዮጵያ ትበተናለች በሚል ምክንያት ሕዝባችን ለኢትዮጵያ አንድነት ሲባል በመስዋዕት በግነት ሲያቀርቡት ቆይተዋል። በዚህ ምክንያት ብዙ ዋጋ ከፍለናል።

እነዚህ ወገኖች የአማራን መደራጀት አጥብቀው ይቃወማሉ። ዋናው ምክንያታቸው በአማራ ሕዝብ መስዋዕትነት የኢትዮጵያን አንድነት መጠበቅ ቢሆንም፣ የሚያቀርቡት መከራከሪያ ግን የተለያየ ነው። ‹በአማራነት መደራጀት ጠባብ መሆን ነው፤ የወያኔን አጀንዳ መፈጸም ነው፤ አማራ የሚባል ብሔር የለም› ወዘተረፈ እያሉ ውኃ የማይቋጥር፣ ነገር ግን ሕዝባችንን ትጥቅ የሚያስፈታ አስተያየት ይሰነዝራሉ። እነዚህ አካላት የአማራ ሕዝብ ከያለበት ሲሳደድና ልጆቹን በግፍ ሲነጠቅ ይህ ነው የሚባል እንቅስቀሴና ድጋፍ አድርገው አያውቁም። ነገር ግን ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ የአማራን ሕዝብ መደራጀት አጥብቀው ይቃወማሉ። በዚህ ጉዳይ ላይ ከእነዚህ ወገኖች ጋር የማይታረቅ አቋም አለን።

እነዚህ ወገኖች የአማራን ሕዝብ መደራጀት ከመቃወምም አልፈው የሕዝባቸው ጥቃት አንገብግቧቸው ለአማራ ሕዝብ መደራጀት ሌት ተቀን የሚሠሩ ልጆቻችንን ልዩ ልዩ ስም እየሰጡ ማሸማቀቁን ሥራዬ ብለው ተያይዘውታል። ይህ ጸረ አማራ አካሔድ መታረም ይኖርበታል። እነሱ ስለኢትዮጵያ አንድነት እንጨነቃለን ይላሉ። እኛም አባቶቻችን አጥንታቸውን ከስክሰው ስለመሠረቷትና በደማቸው ነጻነቷን ጠብቀው ስላቆዩዋት ኢትዮጵያ ይገደናል። ሆኖም አማራነታችን ይዘን፣ እንደአማራ ተደራጅተን እንጂ እንደከዚህ ቀደሙ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ማለቱ ለሕዝባችን ያበረከተው ነገር በተናጠል መገደልንና መጨፍጨፍን ብቻ ነው ብለን በጽኑ እናምናለን።

ስለዚህ ከእነዚህ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ጋር የጋራ ጠላታችን የሆነውን ወያኔን ለመቅበር መረባረባችን እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ሕዝባችን እንዳይደራጅ የሚያደርጉት ቅስቀሳ አውዳሚና ልንታገሰው የማንችለው ጉዳይ ነውና እነሱንም በዚህ ረገድ መታገላችን ተገቢ ነው እንላለን። አማራ በአማራነቱ እንዳይደራጅ የሚቀሰቅስ ማንኛውም ኃይል ትጥቅ አስፈችና ለማንም አላፊ አግዳሚ ኃይል አሳልፎ የሚሰጠን ስለሆነ አንቀበለውም፤ እንታገለዋለን።

እንግዲህ፣ በእኛ በኩል ግንባር ቀደም ጠላታችን ወያኔ መሆኑን አሳምረን እናውቃለን። ሁሉም ኃይል በዚህ የጋራ ጠላት ላይ መረባረብ እንዳለበትም በሚገባ እንገነዘባለን። ሆኖም ወያኔን ለመቅበርም ሆነ ከወያኔ በኋላ የሕዝባችን ጥቅም ማስከበር የምንችለው እንደሕዝብ፣ እንደአማራ ስንደራጅ ነው ብለን በጥብቅ ስለምናምን በዚህ በኩል መሰናክል የሚፈጥሩብንን ወገኖችም አንታገስም። ወያኔን በመቅበሩ ላይ ብቻ እንረባረብ ማለት ያለብን እኛ ብቻ አይደለንም። እነሱም እኛ የቆምንለትን ዓላማ መጎንተሉን ትተው በዚህ የጋራ አጀንዳ ላይ ብቻ እንዲያተኩሩ ያስፈልጋል። በእኛ በኩል የአማራን ሕዝብ ጥቅም እስካስጠበቀ ድረስ ሁልጊዜም ከአንድነት ኃይሉ ጋር ለመሥራት ዝግጁ ነን።

መ. ከሌሎች ሕዝቦች ጋር ያለንን ሚና እንለይ፤

የአማራ ሕዝብ ለዘመናት ከሌሎች የኢትዮጵያ ሕዝቦች ጋር በአብሮነት ኖሯል። ጸረ አማራ የሆነው የወያኔ ቡድን በሚቆጣጠራቸው መገናኛ ብዙሃን ሲያስተጋባና ሰነድ አዘጋጅቶ ሲሰብክ እንደኖረው ሳይሆን የአማራ ሕዝብ ከየትኛውም የኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ጠብ ኖሮት አያውቅም፤ አሁንም የለውም። ሕዝባችን ከሌሎች የኢትዮጵያ ሕዝቦች ጋር በክፉም በደጉም አብሮ የኖረ ደግ ሕዝብ እንጂ፣ የትኛውንም ዓይነት ጭቆና የማይቀበለው የአማራ ሕዝብ ሌሎችን ሕዝቦች የጨቆነበት ጊዜ እንደሌለ ታሪክ ምስክር ነው። ማንም እንዲጨቁነን የማንፈልገውን ያህል እኛም ማንንም የመጨቆን ዓላማ የለንም፤ ኖሮንም አያውቅም።

እንደሚታወቀው ወያኔ የአማራን ሕዝብ በጨቋኝነት መፈረጅ ብቻ ሳይሆን ሌሎች የኢትዮጵያ ሕዝቦችም ይህንን ጸረ ሕዝብ አስተሳሰብ እንዲቀበሉ በከፍተኛ ደረጃ ቀስቅሶ ቀላል የማይባል ውጤት አግኝቶበታል። ሆደሰፊው ሕዝባችን ግን አሁንም ከሌሎች የኢትዮጵያ ሕዝቦች ጋር በእኩልነት ላይ የተመሠረተ አንድነት መገንባት እንደሚፈልግ፣ ለዴሞክራሲና ለሕዝቦች እኩልነት እንደሚታገል እና የሌሎች ሕዝቦች በደል እንደሚያንገበግበው በማያወላውል መልኩ ገልጿል። ሕዝባችን ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር ሆኖ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን መገንባት እንደሚፈልግ በማያሻማ ሁኔታ አሳይቷል።

ይህ ማለት ግን የአማራ ሕዝብ ከሌሎች የኢትዮጵያ ሕዝቦች ጋር በሁሉም ጉዳዮች ላይ ይግባባል ማለት አይደለም፤ ሊሆንም አይችልም። ከሌሎች ሕዝቦች ጋር የሚያግባቡን በጣም ብዙ አጀንዳዎች ያሉትን ያህል በርካታ ልዩነቶች እንዳሉንም እንረዳለን። ሆኖም ልዩነቶቻችን እንደተጠበቁ ሆነው፣ ወይም ልዩነቶቻችንን አክብረን በሚያግባቡን ጉዳዮች ላይ አብረን መሥራት ደግሞ እንችላለን፤ ይገባናልም።

በእኛ በአማራ ልጆች እምነት የሁሉም የኢትዮጵያ ሕዝቦች ቀንደኛ ጠላት ወያኔ ነው። እንዳንተባበርና እርስ በርሳችን እንድንጠራጠር የሚያደርገንም ይኸው አናሳ የወያኔ ቡድን ነው። ስለሆነም ይህን የሁላችንም ጠላት የሆነ ጸረ ሕዝብ ኃይል ለማንኮታኮት፣ ከላይ እንደተገለጸው ልዩነቶቻችን እንደተጠበቁ ሆነው በሚያስተሳስሩን በርካታ ጉዳዮች ላይ አተኩረን መሥራት እንችላለን፤ ይገባናልም። ሕዝባችን ለዚህ ሁልጊዜም ዝግጁ ነው።

#የአማራ_ተጋድሎ ይቀጥላል!!!

No comments:

Post a Comment

wanted officials