Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Wednesday, November 30, 2016

ፕ/ር መረራ ጉዲና ታፍነዋል


ክንፉ አሰፋ
30 ኖቬምበር 2016 – የመድረክና የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ መሪ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ዛሬ ረቡእ ማምሻውን በደህንነት ሃይሎች ታፍነው መወሰዳቸውን ለማረጋገጥ ችለናል።
Dr.-Merara-Gudina
በዛሬው እለትፕ/ር መረራ ጉዲና መኖርያ ቤት በደህንነቶች እና ከባድ መሳርያ በጣጠቁ የአጋዚ አባላት ተከብቦ መዋሉን የአይን እማኞች ገልጸዋል። ብእር ብቻ ለያዘ አንድ ሰላማዊ ሰው ይህን ሁሉ ሃይል ማሰማራት ስር ዓቱ ምን ያህል እንደተብረከረከ የሚያሳይ መሁኑን እማኞቹ ጨምረው ገልጸዋል።
በአውሮፓ ህብረት ጥሪ ተደርጎላቸው ሃገሪቱ ስላለችበት መስቀለኛ መንገድ ገለጻ አድርገዋል። ከዚያም በሆላንድ፣ በጀርመን እና በስዊዘርላንድ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን ጋር ስለ ሃገሪቱ ሁነታ መወያየታቸው ይታወሳል።
የኢትዮጵያ ችግር በሰላማዊ መንገድ መፍትሄ ያገኛል ብለው በምርጫ እና በሰላማዊ አግባብ ሲታገሉ የነበሩት ፕ/ር መረራ ጉዲና ለምን እንደታፈኑ ግልጽ የሆነ ነገር የለም። ከዶ/ር ብርሃኑ ጋር በአውሮፓ ህብረት ተጋብዘው መገኘታቸው ወንጀል መሆኑን የገዥው ፓርቲ ልሳኖች ሲያረግቡት እንደነበር አይዘነጋም።

No comments:

Post a Comment

wanted officials