Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Sunday, November 27, 2016

ጠቅላይ አቃቤ ህግ ሆነው የተሾሙት አቶ ጌታቸው በከፍተኛ ህክምና ታይላንድ ባንኮክ ይገኛሉ።


በቅርቡ ጠ/ሚኒስትር አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ ባወቀሩት ካቢኔ ውስጥ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ሆነው የተሾሙት አቶ ጌታቸው አምባዬ ከተሾሙበት ጊዜ ጀምሮ በስራ ገበታቸው ላይ አለመሆናቸው ታወቀ። የቅርብ ምንጮች እንደገለጹት ባለስልጣኑ በታይላንድ ባንኮክ በከፍተኛ ህክምና ላይ ይገኛሉ። ሹመቱ የተሰጣቸው በውጭ ሃገር በህክምና ላይ መሆናቸው እየታወቀ መሆኑን መረዳት ተችሏል።
በቅርቡ ጥቅምት 22 ቀን 2009 ዓም በተዋቀረው ካቢኔ ውስጥ በነበሩት ቦታ እንዲቀጥሉ ከተወሰነላቸው ሚኒስትሮች አንዱ የሆኑት አቶ ጌታቸው አምባዬ ብዓዴንን ወልከው ስፍራውን በመያዛቸው፣ ብዓዴን እርሳቸውን የሚተካ ሰው ባለማቅረቡ በህመም ላይ ባሉበት በድጋሚ መሾማቸውም ተመልክቷል።
ጥቅምት 22፣ 2009 ዓም በተዋቀረው ካቢኔ ውስጥ እንደገና በጠቅላይ አቃቤ ህግነት የቀጠሉት አቶ ጌታቸው አምባዬ በ1982 የትጥቅ ትግል የተቀላቀሉና በትጥቅ ትግል እንዳለፉት ሁሉ በልዩ ዕገዛ በከፍተኛ ትምህርት ተቋም መማራቸውን ለማወቅ ተችሏል።
በጥቅምት ወር መጀመሪያ ላይ በአስቸኳይ አዋጁ ዙሪያ ማብራሪያ ሲሰጡ የታዩትና ከዚያ በኋላ በድንገት ጤናቸው ታውኮ በታይላንድ ባንኮክ አንድ ወር ያህል ያስቆጠሩት የአቶ ጌታቸው አምባዬ ህመም ምን እንደሆነ ምንጮች አልገለጹም። ሆኖም ባለስልጣናት ከዚህ ቀደምም በተደጋጋሚ ህክምና ያለፉ መሆናቸውን በመግለጽ ችግሩ የቆየ የጤና ችግር የተያያዘ ሳይሆን እንዳልቀረ አመልክተዋል።
ከአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ወደ አዲስ አበባ ካቢኔ በመጨረሻ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ከፍትህ ሚኒስትርነታቸው በተነሱት የብዓዴኑ አቶ ብርሃን ሃይሌ ምትክ ፍትህ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙ አቶ ጌታቸው አምባዬ፣ ፍትህ ሚኒስቴር ፈርሶ ወደ ጠቅላይ አቃቤህግነት ሲሻገሩም ከነስልጣናቸው ቀጥለዋል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials