Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Wednesday, November 23, 2016

ዶላር በጥቁር ገበያ የሀዋላ ግብይት አስደንጋጭ ጭማሪ አሳየ

ዶላር በጥቁር ገበያ የሀዋላ ግብይት አስደንጋጭ ጭማሪ አሳየ


  • 1274
    Share
  • ክስተቱ በገቢ እቃዎች ዋጋ ላይ ጉልህ ተጽእኖ ሊፈጥር ይችላልImage result for dollar exchange black market
ዋዜማ ራዲዮ- ኢትዮጵያ ለገቢ ንግድየሚቀርቡ የዉጭ ምንዛሬጥያቄዎችንየምታስተናግድበት አቅም ከጊዜወደጊዜ እየተመናመነ መምጣቱንተከትሎአስመጭ ነጋዴዎች ግብይትየሚያደርጉት ከጥቁር ገበያ በሚገዙት የውጭ ምንዛሪ ብቻ እየኾነነው፡፡ ይሁንናአገር ዉስጥ ከጥቁር ገበያ የተገዛንየውጭምንዛሪ ከአገር ይዞ መውጣት ከባድወንጀል በመሆኑ ከፍ ያለ መጠንያለውየዶለር ግዢ የሚካሄደው በአመዛኙበጥቁር ገበያ የሀዋላ ቅብብሎሽ ነው፡፡ 
ከዚህም የተነሳ አሁን አሁን ማንኛውንምየገቢ ንግድ ለማካሄድ  በሀዋላቅብብሎሽየሚገኝ የዉጭ ምንዛሬ ጉልህ ድርሻ እየያዘመጥቷል፡፡ የነጋዴውማኅበረሰብ ሁነኛየዶላር ምንጭም ይኸው ስልት ብቻ እየኾነ ነው ይላሉታዛቢዎች፡፡የጥቁር ገበያ ሀዋላ ቅብብሎሽ ግብይት የሚፈጸመው በዋናነት ዱባይ፣ ቱርክና ቻይናተቀማጭነታቸውን ባደረጉ ኢትዮጵያዊያንባለሐብቶች ምክንያት ገንዘብ በጥሬ ብር አገር ውስጥ ላሉ ወኪሎቻቸው እየተሰጠ በምትኩ ተመጣጣኙንየውጭምንዛሬ ለአስመጪው በዉጭአገር በዶላር እንዲከፈል በማድረግ ነው፡፡ 
ከሰሞኑ ከፍተኛ ጭማሪ አሳየ የተባለውም ለዚሁ ሕገወጥ ግብይት ማስፈጸሚያ የሚከፈለውና በዶላር የሚሰላው የኮሚሽን መጠን ነው፡፡ ይኸው የኮሚሽን መጠን ከሰሞኑ በአንድ ዶላር የሦስት ብር ጭማሪ ማሳየቱ ለአስመጪ ነጋዴዎችስጋት ፈጥሯል።
ምንም እንኳ ይህ የውጭ ምንዛሪን በሀዋላ የመቀባበል ሥርዓት በሕጋዊ መንገድ የውጭ ምንዛሪ የማግኘቱ ጉዳይ አስቸጋሪ ከመኾኑ ጋር ተያይዞለረዥምጊዜ በአስመጪ ነጋዴዎች ዘንድ ሲሠራበት የቆየ ኢመደበኛ ሥርዓት ቢሆንምለአገልግሎቱ ይከፈል የነበረው ዋጋ ይህን ያህል የተጋነነአልነበረም፡፡ ይህክፍያ ዶላር አገር ዉስጥ በጥቁር ገበያ ከሚገዛበት ዋጋ አንጻር ሲታይም ብዙ መራራቅ አልነበረውም፡፡ አሁን ግን በቅብብሎሹሰንሰለት የአንድ ዶላር ዋጋከአንድ ወርበፊት ከነበረበት 24 ብር ተመን በአንድ ጊዜ ወደ 27 ብር አድጓል፡፡
ይህ ዜና በሚጠናቀርበት ወቅት ኢትዮጵያ ዉስጥ በጥቁር ገበያ አንድ ዶላር የመሚገዛበት ዋጋ 26.20 ሳንቲም ደርሷል፡፡ በአንጻሩ አንድ ዶላርከባንክየሚገዛበት ተመን 22 ብር 20 ሳንቲም ብቻ ነው፡፡ ነጋዴዎች የውጭ ምንዛሪውን ከሐዋላአቀባባዮች ሲቀበሉ ግን አንድ ዶላርየሚመነዘረው 27.07ብር ነው፡፡ አስመጪዎች ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ 24 እና 25 ብር ገደማ ይገዙት የነበረው ዶላር አሁን በአንድ ጊዜአስደንጋጭ ጭማሪ በማሳየትከመደበኛው የዶላር ዋጋ 4. 87ብር ልዩነት አሳይቷል፡፡ ይህ አሀዝ ዶላር ከብር ጋር ያለውን እውነተኛ የለውጥ ተመን የሚያመላክት ነው ይላሉ ለጉዳዩቅርብ የሆኑ ታዛቢዎች፡፡  
 አስመጪ ነጋዴዎች በሕጋዊ መንገድ ከባንኮች የሚፈቀድላቸው የዶላር መጠን ካለፈው ዓመት አጋማሽ ጀምሮ እየቀነሰ መጥቶ አሁን ጨርሶውኑየለምበሚባልበት ደረጃ ላይ እየደረሰ ነው፡፡ ይህ ሁኔታ የዶላርን ተፈላጊነት በሀዋላ ገበያበእጅጉ ሳያንረው አልቀረም፡፡ አሁን የታየው ጭማሪምምናልባት የዚህክስተት ተያያዥ ዉጤት ሳይሆን እንዳልቀረ ይገመታል፡፡
በዚህ ወቅት ይቅርና ወትሮም ዶላር በተሻለ ፍጥነትና መጠን ከባንኮች በሚገኝበት ዘመን ወደ ሀዋላ ቅብብሎሽ ዘዴ መሄድ የተለመደ እንደነበርየሚናገሩነጋዴዎች ባንኮች ዶላር መስጠት በማቆማቸው የጥቁር ገበያው ዋጋ ከዚህም በላይ እንዳይንር ስጋት ገብቷቸዋል፡፡ ብዙዉን ጊዜ ነጋዴዎችወደ ሐዋላ ጥቁርገበያ ፊታቸውን የሚያዞሩት ዕቃ ለማስመጣት የሚያስፈልጋቸውን የገንዘብ መጠን ከሕጋዊ ባንኮች መቶ በመቶ ተሟልቶስለማይሰጣቸው ነው፡፡ 
በአንጻሩ ከመንግስት ጋር ቅርርብ ያላቸው ጥቂት አስመጪዎች ወደ አገር ዉስጥ ለሚያስገቡት ዕቃ ከብሔራዊ ባንክ የዋስትና ሰነድ (Letter of Credit) በመክፈት ሲነግዱ ይታያል ፡፡ ኾኖም የሚያስመጡት ዕቃ የውጪ ምንዛሪውን ገበያ ከፍናዝቅ ከማድረጉም በላይ በልዩነቱ የሚያገኙትንየውጭምንዛሬ በሕገወጥ መንገድ ከአገር እንዲወጣ በማድረግ ገንዘቡን ለጥቁር ገበያ የሐዋላ የዶላር ቅብብሎሽ ሲያውሉት ይታያል፡፡ ይህ የዉጭምንዛሬን ከአገርማሸሽ (Capital Flight)ይበልጥ የሚስተዋለው አገሪቱ መረጋጋት በራቃት ጊዜ ከባለሥልጣናት ጋር እጅና ጓንት ኾነው በሚሰሩነጋዴዎች ዘንድእንደሆነም ይታማል፡፡  
ለዋዜማ ጥቆማቸውን የሰጡ መደበኛ አስመጪዎች እንደሚሉት ከዚህ ቀደም ወደ ሕገወጥ የሐዋላ ቅብብሎሽ የሚኬደው የጎደለ የዉጭ ምንዛሬለማሟላትብቻ ስለነበር እንደአሁኑ የተጋነነ ፍላጎት ሳይከሰት ቆይቷል፡፡ ለአገልግሎቱየሚጠየቀው መጠንም እንደአሁኑ ከፍ ያለ አልነበረም፡፡ አሁንበአንድ ጊዜ ከፍያለ የዶላር መጠን ከብዙ ነጋዴዎች ወደ ሀዋላ አቀባባዮች ዘንድ መቅረቡ የኮሚሽን ንረቱ እንዲፈጠር ምክንያት እንደሆነይገምታሉ፡፡
ዋዜማ በስልክ ያነጋገረቻቸው አገር ቤት የሚገኙ የአስተላላፊ ወኪሎች ጭማሪው ለምን እንደተከሰተ የተሟላና አጥጋቢ ምላሽ ለመስጠትተቸግረዋል፡፡ከፊሎቹ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ተከትሎ የተፈጠረ ጊዜያዊ ችግር እንደሆነና ፖለቲካዊ መረጋጋት ሲፈጠር ስሌቱም አብሮ እንደሚረጋጋይገምታሉበአንጻሩ ገንዘባቸውን እያሸሹ ያሉ ባለሐብቶች በመበርከታቸው የተፈጠረ ችግር አድርገው የሚቆጥሩትም ነጋዴዎች አሉ። ነጋዴዎቹእንደሚሉት ውጭአገር የሚገኙ ዶላር አቀባባዮች በቁጥር ውስን በመሆናቸው በተመሳሳይ ወቅት በርካታ የውጭ ምንዛሪ ፈላጊዎች ከአገር ቤትሲጎርፉባቸው ፍላጎቱንለሟሟላት ሲሳናቸው ይስተዋላል፡፡ ይህም የሚሆነው የአቀባባዮቹ አቅም ከሚፈለገው የውጭ ምንዛሪ መጠን ጋር ሲነጻጸርውስን በመኾኑ ምክንያት እንደኾነ አስመጪዎቹ ይናገራሉ፡፡
በጉዳዩ ላይ አስተያየቱን የሰጠ አንድ የቡና ባንክ የምጣኔ ሀብት ባለሞያ በበኩሉ የኮሚሽን ንረቱ ምክንያት የዉጭ የሀዋላ አስተላላፊዎችየፍላቱንመጨመር ተከትሎ የሚፈጥሩት ጊዜያዊ ችግር እንደሆነ ይገምታል፡፡ እነሱ ዶላርለሚጠይቋቸው ነጋዴዎች  የሚከፍሉት የዉጭ ምንዛሬባነሳቸውቁጥር ትርፋቸውን በመቆለል ጥያቄዉን ለማስታገስ ይሞክራሉ የሚል ግምት አለው።
አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ኢትዮጵያ ዉስጥ ማንኛውም አስመጪ እቃ የሚገዛው የተመን ቅናሽ (UnderInvoice) በማስደረግ ነው፡፡ ይህሊሆንየቻለው ገቢን ደብቆ የቀረጥ ተመንን ለማሳነስ ብቻ ሳይሆን የተጠየቀውን ያህል የዉጭምንዛሬ በተፈለገው ጊዜ ማግኘት ፈጽሞ ስለማይቻልነው፡፡ 
አንድ ኮንቴይነር ሙሉ ዕቃ 10 ሺህ ዶላር አስመጣሁ ትላለህ፡፡ዕቃው ከመቶ ሺህ ዶላር በላይ እንደሚፈጅብህ ግን አንተምመንግሥትምታውቃላችሁ፡፡ የተፈቀደልህ ዶላር 10ሺህ ብቻ እንደሆነ መንግሥት እያወቀ “ቀሪዉን ዶላር ከየትአምጥተህ ነው ይህን ሁሉ እቃ የገዛኸው?ብሎአይጠይቅህም፡፡” ይላል ለዋዜማ አስተያየቱን የሰጠ አንድ የወረቀት አስመጪ፡፡
 “ዞሮ ዞሮ መንግሥት እውነታውን እያወቀ የተደነገገውን የዋጋ ተመንን በማመሳከር ብቻ ገቢዎችና ጉምሩክ ይቀርጥኻል፡፡ ለእያንዳንዱ እቃአነስተኛ የትርፍተመን አስቀምጦ ከዚያ በታች እንዳትሸጥ ይመክርሃል፡፡ በዚያ የትርፍ ምህዳርእንደማትሸጠው ግን አንተም መንግሥትምበልቦናችሁ ታውቃላችሁ፡፡” ሲልየድብብቆሹን ርቀት ያብራራል፡፡ 
መንግሥት የዶላር እጥረት የለብኝም ይላል፡፡ እኔ የሕብረት ባንክ ተበዳሪ ነኝ፡፡ ለምንዛሬ ካመለከትኩ ስድስት ወር አልፎኛል፡፡ የጠየቅኩትን ዶላርሩቡንእንኳ አልሰጡኝም፡፡ ተበዳሪ ምንዛሬ ወረፋ ላይ ቅድሚያ እንዲያገኝ ይደረጋል፡፡ካልነገድኩና ነግጄ ካላተረፍኩ የተበደርኩትን መመለስእንደማልችልያውቃሉ፡፡ ዶላር የማይሰጡኝ ስለሌላቸው ነው፡፡ ዶላር ቢኖራቸው ከማንም በፊት ለኔ እንደሚሰጡኝ አውቃለሁ” ይላል ዋዜማያነጋገረችው ይኸውአስመጪ፡፡  
የዶላር ሀዋላ ቅብብሎሹን በተመለከተ ሲያስረዳም “መቶ ሺህ ዶላር ለገቢ ንግድ የፈለገ ነጋዴ 10ሺህ ዶላር በሕጋዊ መንገድ ከባንክ ቢያገኝየተቀረውን90 ዶላር ማግኘት የሚችለው ከሀዋላ አስተላላፊዎች ብቻ ነው” ይላል፡፡  “ለዚህ ነው በእምነት ላይ ብቻ ለተመሰረተ የገንዘብምንዛሬ ልዉዉጥ አገርቤት በብር ከፍተኛ ኮሚሽን መክፈል የሚኖርበት” ካለ በኋላ እቃውን ለማስገባት ማግኘት ያለበትን 90ሺህ ዶላርለማግኘት  ሦስት መቶ ሺህ ብር በላይለአስተላላፊዎችበኮሚሽን መልክ ለመክፈል እንደተገደደ ይዘረዝራል፡፡ ባንክ የጠየቅኩትን ምንዛሬቢያቀርብልኝ ኖሮ ይህን 3መቶ ሺህ ብር ማዳን እችልነበር ይላል፡፡
የቡና ባንክ የምጣኔ ሀብት ባለሞያው በበኩሉ “ይህ የምትለው አይነት ጭማሪ በጥቁር ገበያ በእውን ተከስቶ ከሆነ ተጽእኖው በጊዜ ሂደትየሸቀጦች ዋጋላይ መታየት አለበት” ይላል፡፡ “ነጋዴዎች ይህን ወጪ የሚያካክሱት ትርፋቸውንበመቀነስ ሳይሆን በሸማቾች ላይ ዋጋ በመቆለልእንደሆነ አስረግጦከተናገረ በኋላ “ምናልባት ነገሮች ካልተሻሻሉ መንግሥት የዉጭን ንግድን ለማበረታታት ከዚህ ቀደም አድርጎት እንደነበረው ብርከዶላር ጋር ያለውንልዩነት ለማስፋትመገደዱ  አይቀርም” ይላል፡፡
በርካታ የምጣኔ ሀብት ባለሞያዎች እንደሚያምኑት ኢመደበኛ የዉጭ ምንዛሬ ግብይቶች መስፋፋት የአንድን አገር ምጣኔ ሀብት አለመረጋጋትሊጠቁምይችላል፡፡ በተለይም በጥቁር ገበያና በመደበኛው የዉጭ ምንዛሬ ግብይት መካከልያለው ልዩነት እየተራራቀ መሄድ መልእክቱ ጥሩ ዜናንይዞ የሚመጣአይደለም፡፡
ለምሳሌ ጥቁር ገበያው ተጽእኖ እያየለ ሲመጣ የባንኮችን የገንዘብ ክምችት አደጋ ላይ ስለሚጥል አሳሳቢነቱን ያጎላዋል፡፡ ሰዎች የዉጭ ምንዛሬንለማግኘትባለው ኢመደበኛ መንገድ ሁሉ በመሄድ፣ የተጋነነ ክፍያ ጭምር በመፈጸም ዶላርንማሳደድ ይጀምራሉ፡፡ ይህን ለማድረግ በባንክያከማቹትን ገንዘብለማውጣት ይገደዳሉ፡፡ ይህም የባንኮችን ካዝና ያመናምናል፡፡ የባንኮች ጥሪት ሲመናመን ደግሞ የብድር አቅርቦት ላይ አሉታዊተጽእኖ ስለሚኖረውኢንቨስትመንትንይጎዳል፡፡ 
የዉጭ ምንዛሬ ግብይቱ ወደ ጥቁር ገበያው እያመዘነ መሄድ ባንኮች ላይ የሚኖረው ተጽእኖው በዚህ ብቻ አያበቃም፡፡ ወደ አገር ዉስጥ የሚገባየዉጭምንዛሬ መደበኛውን መስመር ስለማይከተል ባንኮች ከዉጭ ምንዛሬ ሊያገኙት ይችልየነበረውን ጥቅም ይጎዳባቸዋል፡፡ እንደማሳያምከዓመታት በፊት የግልባንኮች ከሚያገኙት ትርፍ ከፍተኛውን እጅ ይይዝ የነበረው ከዉጭ ምንዛሬ ሽያጭ የሚገኝ ገቢ ነበር፡፡ ከሰሞኑ የትርፍመጠናቸውን ይፋ ያደረጉ በርካታየግል ባንኮችመረጃ እንደሚያመለክተው ደግሞ ገቢያቸው ካለፉት ዓመታት ቅናሽ ሊያሳይ የቻለው የቋሚወጪዎቻቸው መጨመርና የዉጭ ምንዛሬግብይት መቀዛቀዝ በመኖሩ ነው፡፡ ባንኮች ከጥቂት ዓመታት በፊት ለአክስዮን አባሎቻቸውይከፍሉትየነበረው የትርፍ መጠን 40 በመቶ በላይ የነበረሲሆ አሁን ግን ወደ 27 በመቶ ወርዷል፡፡
ለዚህ አስደንጋጭ ነው ለተባለለት የዶላር የሐዋላ ቅብብሎሽ የኮሚሽን መጠን ማሻቀብ ከሰሞኑ በአገር ዉስጥ የጥቁር ገበያ ነጋዴዎች ላይየተካሄደውዘመቻ ሌላው ምክንያት እንደሆነ የሚጠረጥሩም አልጠፉም፡፡ የፌዴራል ፖሊስከሳምንታት በፊት ጥቁር ገበያ ላይ ተሳትፎ እንዳላቸውበሚታመኑግለሰቦችና አካባቢዎች ላይ ድንገተኛ አሰሳ ማካሄዱ አይዘነጋም፡፡

No comments:

Post a Comment

wanted officials