Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, November 15, 2016

በደቡብ ኢትዮጵያ በስሎቫኪያና ቼክ ሪፐብሊክ ቱሪስቶች ላይ ጥቃት መፈጸሙ ተገለጸEthiopia: Tourists attacked, driver killed

Ethiopia: Tourists attacked, driver killed


mizan-teferi-10ESAT News (November 14, 2016)
A group of tourists were reportedly attacked and robbed in southern Ethiopia last week and their driver was shot and killed, according to a report by The Slovak Spectator, Slovakia’s only English-language newspaper.
The six Slovaks and four Czechs were attacked in the town of Mizan on November 7. They were robbed of their credit cards, money and other precious possessions. Irena Valentová from the Czech Foreign Affairs Ministry confirmed the incident to Novinky.cz website. She was quoted as saying that a female Slovak tourist was injured in the attack.
The attackers shot an Ethiopian driver during the incident who died at the hospital. Head of the Bubo Travel Agency, Ľuboš Fellner, whom the Czech website cited, said the incident occurred in the so-called green zone considered to be fully safe.
The Slovak Foreign Ministry confirmed the case for the TASR newswire on November 11, adding that the Slovak tourists were provided with new travel documents and to return home.
The Foreign Ministry recently warned Slovak citizens not to travel to Ethiopia, due to a worsened security situation that resulted in a state of emergency starting October 8, for six months.  
Ethiopian authorities, in an attempt to encourage tourists to visit the country, issued a statement saying the state of emergency does not restrict tourists and that tourists could go anywhere without prior notice to the government.
The authorities, having seen a sharp decline in tourism, have issued a directive lifting the ban imposed by the state of emergency on diplomats that prohibits travel beyond 40 kilometers (25 miles) radius outside the capital.
Ethiopia is expected to lose about 400 million dollars from tourism in the current budget year due to the unrest in the country.
The Ethiopian Culture and Tourism Minister said that in the last three months alone the country’s income from tourism has shown a decline by 7.4 million dollars.
The country had planned to generate 3 billion dollars from tourism this year but that could be far fetched due to the political crises in the country, according to the Ministry.

ኢሳት (ህዳር 5 ፥ 2009)
በደቡብ ክልል ሚዛን ከተማ አካባቢ በጉብኝት ላይ የነበሩ 10 የስሎቫኪያና የቼክ ሪፐብሊክ ቱሪስቶች ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች ዝርፊያ ተፈጽሞባቸው ሹፌራቸው መገልደሉ ተገለጸ።
የቼክ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከቀናት በፊት በክልሉ ጉብኝት በማድረግ ላይ የነበሩት ቱሪስቶች በታጠቁ ሃይሎች ገንዘብን ጨምሮ የባንክ መገልገያ ካርዶችና ሌሎች ንብረቶቻቸው እንደተወሰደባቸው ሰኞ ይፋ አድርጓል።
የቼክ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተወካይ የሆኑት ኢሬና ቫሌንቶባ፣ ዝርፊያ ከተፈጸመባቸው የቼክ ተወላጆች መካከል አንድ ሴት ጉዳት እንደደረሰባት ለሃገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ገልጸዋል።
ቱሪስቶችን በማጓጓዝ ላይ የነበረ ማንነቱ ያልተገለጸ አንድ ሹፌር በተተኮሰበት ጥይት ጉዳት ደርሶበት ለህክምና ቢወሰድም ህይወቱ ማለፉን አሶሼይትድ ፕሬስ የቼክ ውጭ ጉዳይ ባለስልጣናትን ዋቢ በማድረግ ዘግቧል።
በኢትዮጵያ ተግባራዊ ተደርጎ የሚገኘውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተከትሎ ወደ ኢትዮጵያ የሚጓዙ የቱሪስቶች ቁጥር በከፍተኛ መጠን መቀነሱ ሲገለፅ ቢቆይም መንግስት ቱሪስቶች ያለምንም የደህንነት ስጋት ወደፈለጉት ስፍራ መጓዝ ይችላሉ ሲል ማስታወቁ ይታወሳል።
ይሁንና መንግስት ለቱሪስቶች ማረጋገጫን ቢሰጥም በአስሩ ቱሪስቶች ላይ በደቡብ ክልል ሚዛን ኣከባቢ የተፈጸመው ዝርፊያ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑ ታውቋል።
የስሎቫኪያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ ዝርፊያ የተፈጽሞባቸውን ስድስት የሃገሪቱ ዜጎችን ወደ ሃገራቸው መመለሱን አስታውቋል።
በኢትዮጵያ ተግባራዊ ተደርጎ የሚገኘውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተከትሎ የስሎቫኪያ መንግስት ዜጎቹ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይጓዙ አሳስቦ እንደነበር ታሰር የተሰኘ የሃገሪቱ የመገናኛ ተቋም ሰኞ ዘግቧል።
በአለም አቀፍ ቱሪስቶች ላይ የተፈጸመውን ዘረፋና የሹፌሩን ግድያ በተመለከተ የክልሉም ሆነ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እስካሁን ድረስ የሰጡት ምላሽ የለም።
በርካታ የብሪታኒያ አስጎብኚ ድርጅቶች በኢትዮጵያ ተግባራዊ ተደርጎ ያለውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክንያት በማድረግ ወደ ሃገሪቱ ሊያደርጉ የነበሩ ጉብኝቶች እንዲሰርዙ ማድረጋቸው ይታወቃል።
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ኮሚሽን ባለፉት ሶስት ወራቶች ብቻ ከቱሪስት ገቢ ሰባት ሚሊዮን ዶላር ቅናሽ መታየቱን ሰሞኑን ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ በአስሩ ቱሪስቶች ላይ የተፈጸመው ዝርፊያ በጎብኚዎች ላይ ስጋትን ያሳድራል ተብሎ ተሰግቷል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials