Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Wednesday, July 15, 2015

በሕወሓት $5 ሺህ ዶላር የተደለለው ድምፃዊ ደረጀ ደገፋው በዲሲ ከፍተኛ መገለል እየደረሰበት ነው

ቢሆነኝ ከዋሽንግተን ዲሲ

Dereje Degefaw
 የሕወሓት መንግስት በሰሜን አሜሪካ ያሉ ኢትዮጵያውያንን ለመከፋፈል የኢትዮጵያ ስፖርት ፌዴሬሽን በሰሜን አሜሪካ ላይ አንጃ በመፍጠር በስርዓቱ ደጋፊ በሼህ መሀመድ አላሙዲ ሌላ ፌዴሬሽን አቋቁመው በኢትዮጵያውያን ቦይኮት መደረጋቸው ይታወሳል:: ከአንድ ዓመት በፊት የወያኔ መንግስት በሚኒሶታ ባዘጋጀው የስፖርት ፌስቲቫል ላይ ትናንት ሃገር ወዳድ በመምሰል ስለታማኝ በየነ ጀግንነት እያወደሰ ሲዘፍን የነበረው ድምፃዊ ደረጀ ደገፋው ከአላሙዲ የተከፈለው 5 ሺህ ዶላር በልጦበት ሃገር ወዳዱን ኢትዮጵያዊያን ክዶ ተገኝቶ ነበር:: ይህ ድምፃዊ ለገንዘብ ራሱን በማስገዛቱ እጅጉን በ”መጸጸቱ” በዲሲ ባሉ ራድዮኖችና ዲሲን መሠረት ባደረጉ ሚድያዎች እንዳይዘገብበት አርቲስት ታማኝ በየነ እና አበበ በለው እግር ስር መውደቁ ይነገራል:: በወቅቱ የደረጀ ደገፋው ለገንዘብ ሲል ለወያኔ ፌስቲቫል ማድመቂያ መሆኑን እነዚሁ ሚድያዎች ዝም ብለውለት አለፉ:: ሆኖም ግን ሕዝቡ ዝም አላለም:: ይበላበት የነበረበት ሬስቶራንትና የሚውልበት አካባቢ ያሉ ኢትዮጵያውያን ለገንዘብ ሲል ለወያኔ ራሱን የሸጠ እያሉ ማግለል ጀመሩ:: ድምፃዊው ቀጥሎም የአምናው ሳያንስ ዘንድሮም ሕወሓት በአላሙዲ ስፖንሰርነት ዴንቨር ላይ ባደረገውና ቦይኮት በተደረገው ኳስ ጨዋታ ላይ ዘፍኖ ተመልሷል:: ትናንት እነ አቦነሽ አድነውን ቦይኮት አስደርገው ሬስቶራንቷን እንድትዘጋ ያደርጉ የዲሲ ራድዮ ጣቢያዎችና አክቲቭስቶች ደረጀ ደገፋውን ዝም ቢሉትም ሕዝቡ ግን ድምፃዊውን ከማግለል አልተመለሰም:: በዲሲ ብዙ ጊዜ ከሚዝናናበት ካፌ ከሕዝቡ በሚደስበት ተቃውሞ ለመቅረት ተገዷል:: በአሁኑ ወቅት ይህ ድምጻዊ ራሱን ከኢትዮጵያውያን እየደበቀ ለታማኝ ዘፍኖ ያገኘውን ክብር በሕወሓት $5 ሺህ ዶላር ሸጦታል:: ማሳሰቢያ በተለይ ለዲሲ ራድዮኖችና አክቲቭስቶች:- ከወያኔ ጋር ያበረውን ድምፃዊም ሆነ አርቲስት ቦይኮት ማድረጋችሁን እኮራበታለሁ:: ሆኖም ግን ከአንድ አካባቢ ነው የመጣነው በሚል ከወያኔ ጋር ያበረውን አርቲስትም ዝም አትበሉት:: ዘር ቆጠራ ውስጥ ከገባችሁ እናንተም ከወያኔ አትሻሉም::

No comments:

Post a Comment

wanted officials