Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Sunday, July 19, 2015

አርበኞች ግንቦት 7 በወልቃይትና አርማጭሆ መሬቶች ላይ እየተደረገ የሚገኘው ጦርነት በህዝቡና በህወሓት መካከል ሆኗል አለ

arebegnoch
የአርበኞች ግንቦት 7 ራድዮ እንደዘገበው: * ‪‎የተጀመረው‬ የነፃነት ትግል በኢትዮጵያ መሬት ላይ በህዝቡ መካከል ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ * የህወሓት‬ አገዛዝ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ሲፈፅመው የቆየው እስር፣ አፈና፣ ግድያ፣ ማንገላታት፣ ማሸበርና ማፈናቀል በነፍጥ የሚደረገው ትግል ከተጀመረ ወዲህ በእጅጉ ከፍቷል፡፡ ሁለገብ የትግል ስልት የሚከተለው አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ በጠብመንጃ ስልጣን ጨብጦ በመንግስትነት ስም የኢትዮጵያን ህዝብ አፍኖ እየገዛ እና አንጡራ ሀብቱን ከገደብ በላይ እየመዘበረ የሚገኘውን ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ የተባለ ዘረኛ ቡድን ከመመካትም አልፎ በሚያመልከው ጠብመንጃ ደምስሶ በምትኩ ህዝባዊ መንግስት እንዲመሰረት ለማድረግ በበረሃ የጀመረው የትጥቅ ትግል በኢትዮጵያ መሬት ላይ በህዝቡ መካከል አንድ እግሩን በአስተማማኝ ሁኔታ ተክሏል፡፡ መላ ኢትዮጵያን ከጫፍ እስከ ጫፍ በሸፈነ መልኩ በቅርቡ ለሚደረገው የህወሓትን ጎጠኛ ቡድን በኃይል ጠራርጎ ከአገራችን ምድር የማስወገድ ጦርነት የነፃነት ትሉ ብቸኛ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ሙሉ በሙሉ እንዲሳተፍ እና በበላይነት እንዲመራው የሚያስችሉ ህወሃትን ህልውና በማሳጣት ግብአተ መሬቱን የሚያፋጥኑ ሰፊና ጥልቅ ተግባራት በመከናወን ላይ ናቸው፡፡ ሰኔ 25 2007 ዓ.ም በወልቃይት የተጀመረው ህወሓትን የማድማትና ከስሩ የመገዝገዙ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ወደ አርማጭሆ ተስፋፍቶ ህዝባዊነትን በተላበሰ ሁኔታ የማውደም ስልቱን እየቀያየረ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ አርበኞች ግንቦት 7 ሉኣላዊ የስልጣን ባለቤት እንዲሆን የሚታገልለት የኢትዮጵያ ህዝብም የትግሉ ባለቤትና መሪ ሊሆን የሚችልበት ምቹ ሁኔታ ተፈጥራል፡፡ በመሆኑም በአሁኑ ወቅት በወልቃይትና አርማጭሆ መሬቶች ላይ እየተደረገ የሚገኘው ጦርነት በህዝቡና በህወሓት መካከል ሆኗል፡፡ በአካባቢው ህወሓት ሲያደርሰው በቆየው ግፍና በደል ተማረው ከፋኝ ብለው ነፍጥ በማንሳት ጫካ ገብተው የሸፈቱት ገበሬዎች በአርበኞች ግንቦት 7 ጥላ ስር በአንድነት እየተሰባሰቡና በአንድ ዓላማ ተሳስረው የነፃነት ፍልሚያውን አጋግለውት ይገኛሉ፡፡ ህወሃት መራሹ የመከላከያ ሰራዊት በያቅጣጫው በሚደርስበት የደፈጣ እና ድንገተኛ ጥቃት መድረሻው ጠፍቶበት እየታመሰ ይገኛል፡፡ በሰራዊቱ መካከል እርስበርስ አለመተማመን እያየለ ከመምጣቱ በተጨማሪ ሽሽትና መክዳት የዕለት ከዕለት ተግባሩ ሆኗል፡፡ በመላው ኢትዮጵያ ብልጭ ድርግም ሲል የቆየው የፀረ ህወሓት ትግል ንቅናቄ ችቦ ተለኩሶ መንቀልቀል በመጀመሩ ህዝቡ በየአካባቢው ያለማንም አነሳሽ በራሱ ውስጥ ለውስጥ እየተደራጀ ለአይቀሬውና የመጨረሻው ፍልሚያ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡ አርበኞች ግንቦት 7 በህወሓት ላይ ወታደራዊ እርምጃ መውሰድ ከጀመረ ወዲህ ቁጥር ስፍር የሌላቸው ወጣቶች የትጥቅ ትግሉን በመቀላቀል ላይ ናቸው፡፡ ከአገር ውስጥም ሆነ ከአገር ውጭ የእንቀላቀል ጥያቄ የሚያቀርቡ ኢትዮጵያዊያን ቁጥር በጅጉ በመጨመሩ አርበኞች ግንቦት 7 አዳዲስ ታጋዮችን የመቀበሉ ተግባር ከአቅሙ በላይ እየሆነበት መጥቷል፡፡ አርበኞች ግንቦት 7 በኢትዮጵያ መሬት ላይ በህዝቡ መካከል እያደረገ ከሚገኘው ጦርነት ጎን ለጎን ከመተማ እስከ ጎጃም እንዲሁም አርባ ምንጭ ድረስ የድርጅቱን ህዝባዊ ዓላማና የትግል ጥሪ የያዙ በራሪ ወረቀቶችን አሰራጭቷል፡፡ የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ቡድን በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ለ24 ዓመታት ሲፈፅመው የቆየውን መጠነ ሰፊ ሽብር አሁንም በተለይም ደግሞ አርበኞች ግንቦት 7 እርምጃ መውሰዱን ተከትሎ በከፋ ሁኔታ አጠናክሮ ቀጥሎበት ይገኛል፡፡ ህወሓት በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች ታማኝ የሚላቸውን ደህንነቶቹንና የታጠቁ ቡድኖቹን አሰማርቶ ህዝቡን በተለይም ደግሞ ወጣቶችን እያፈነ ወደ ስውር ማጎሪያው በመውሰድና ሰቆቃ በመፈፀም ተግባር ከመጠመዱ አልፎ ሌላ ጭምብል በማጥለቅ ህዝብ ጨፍጭፎ የህዝብ ድጋፍ ለማግኘት ስውር ሴራ መጠንሰሱን ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት ቢሮ አፈትልኮ የወጣው መረጃ አጋልጧል፡፡ ከህወሓት የደህንነት ቢሮ ታማኝ ምንጮች የተገኘው መረጃ እንደሚያረጋግጠው ህወሓት በጎንደርና አካባቢው በጦር አውሮፕላን ህዝብ በመጨፍጨፍ በአርበኞች ግንቦት 7 እና በኤርትራ መንግስት የማላከክ ስውር ዕቅድ ነድፎ አሳቻ ሰዓት እስኪያገኝ እየተጠባበቀ አድብቶ ይገኛል፡፡ -

No comments:

Post a Comment

wanted officials