Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, July 13, 2015

በሰሜን የአገሪቱ ክፍል የሚታየውን ውጥረት ተከትሎ አየር ሃይል በጠንቀቅ እንዲቆም ታዘዘ



ሐምሌ ፫ (ሶስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ባለፈው ሳምንት የአርበኞች ግንቦት7 በወሰደው ፈጣን ጥቃት በርካታ የኢህአዴግ ወታደሮች መገደላቸውን ፣ ይህንን ተከትሎ የወልቃይትና አካባቢው ህዝብ ያሳያው ድጋፍ እና ሽምቅ ተዋጊዎችን ለመቀላቀል የሚጠይቀው ወጣት መበራከት ያሰጋው ገዢው ፓርቲ፣ የአየር ሃይል አባላት በጠጠንቀቅ እንዲቆሙ ማዘዙን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።



Photo File


የአየር ሃይል አባላቱ ካለፉት ሁለት ወራት ጀምሮ ቅዳሜና እሁድ እንዲሁም በሌሊት ፈረቃ እንዲሰሩ ሲደረግ ቢቆይም፣ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ስልጠናው ተጠናክሮ መቀጠሉን እንዲሁም አየር ሃይል አባላቱ ማንኛውም ግላዊ እንቅስቃሴያቸው እንዲገታ ተደርጓል።



የአየር ሃይል አባላቱ ” አንደኛ ደረጃ ተጠንቀቅ” የሚተላለፈው ፓርላማው የጦር አዋጅ ሲያውጅ ብቻ መሆኑን ለኢሳት ቢገልጽም፣ ጠ/ሚኒስትሩ ” ህዝብ አስፈቅደን በኤርትራ ላይ እርምጃ እንወስዳለን ከማለት ውጭ” የጦርነት አዋጅ እንዲታወጅ አላደረጉም።

አዲስ የጦር አውሮፕላኖች ተገዝተው መምጣታቸውንም የደረሰን መረጃ ያመለክታል። በደፈጣ ውጊያ ፈጣን ጥቃት በመፈጸም ከፍተኛ ድል ያገኘው የአርበኞች ግንቦት7 ጦር ፣ በተለያዩ አካባቢዎች እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑንም የሚደረሱን መረጃዎች ያመለክታሉ።

የኢህአዴግ መንግስት ከአንድ ሳምንት ዝምታ በሁዋላ ሰሞኑን ጦርነት እንደነበር ለማመን ተገዷል። በምእራብ ትግራይና ሰሜን አማራ ድንበር ሰርገው ለመግባት የሞከሩ 30 የሻእቢያ ተላላኪዎች ተደምስሰዋል ሲል የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄ/ል አሰፋ ተናግረዋል። ጄኔራሉ ጦርነቱ ከማን ጋር እንደተካሄደ ለመግለጽ ድፍረቱን አላገኙም። በደፈናው የሻእቢያ ተላላኪዎች ከማለት ውጪ አርበኞች ግንቦት7 ለማለት አለመድፈራቸው እንዲሁም “አንድም ያፈገፈገ ተንኳሽ የለም” ካሉ በሁዋላ፣ ተመልሰው “አብዛኞቹን ደምስሰናቸዋል ፣ ጥቂቶችም ይዘናቸዋል” ማለታቸው እርስ በርሱ የሚጋጭ እና የመገለጫውን ተአማኒነት ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ መሆኑን ዘጋቢያችን ገልጿል።
አሰማርቷል። ይሁን እንጅ ለጥበቃ ከተሰማሩት መካካል የተወሰኑ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ጠፍተው ኤርትራ ገብተዋል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials