Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Saturday, July 18, 2015

የጎንደርና የትግራይን ጠረፍ የዘለለዉ ጦርነት ተጧጡፎ ቀጥሏል።

ዜና ዓውደ ውጊያ፥
የጎንደርና የትግራይን ጠረፍ የዘለለዉ ጦርነት ተጧጡፎ ቀጥሏል።
=============================================
ዛሬ የወያኔ ወታደራዊ ደህንነት ቢሮ ከቁጥጥሩ ዉጭ የሆነ ከበድ ያለ ዉጊያ እንደገጠመው በመጥቀስ የድጋፍ ጥሪ ቢጠይቅም ከመከላከያ ሰራዊት ዘመቻ መምሪያ ክፍል መልስ አለማግኘቱ ተሰምቷል፤
ሰሜን ጎንደርና ትግራይ ያልተጠበቁ ስፍራዎች በጦርነት እየታመሱ ሲሆን አርማጭሆና ወልቃይት ጠገዴ ለወያኔ የሚቀመስ አልሆነም።
የወያኔ ቅጥረኛ ወታደሮች መከላከል አቅቷቸዉ ፌደራል ፖሊስና ልዩ ሃይሎች እንዲያግዟቸዉ ከበላይ ወታደራዊ አስተዳደር ቢታዘዙም የተፈለገዉን ያህል መከላከል አልተቻለም።
አርበኞች ግንቦት 7 ሽምቅ ውጊያዉን በብቃት እየተወጣ በሚገኝበት በትናንትናዉና በዛሬዉ እለት ከራሱም ወታደሮቹ እየተስዉበት ይገኛሉ።
የወያኔ መንግሥት ኦባማ መጥቶ እስኪሄድ የጦር ሜዳ ሽንፈቱን ለመደበቅ ሲል ብቻ ቁስለኛ ወታደሮችን ወደ ከተማ ወስዶ ህክምና መስጠት ባለመፈለጉ ወታደራዊ ካምፖች ውስጥ ጊዜያዊ የህክምና ጥላዎችን ዘርግቶ ቁስለኞችን እያጉላላ ይገኛል።
ድል ለአርበኞች ግንቦት 7!!


No comments:

Post a Comment

wanted officials