Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Wednesday, July 15, 2015

በአገርቷ ሁሉ ያሉ የቶርቸር እሥር ቤቶች የወያኔን ጭካኔ ነው የሚያሳዩት – የሚሊዮኖች ድምጽ



የወያኔው ሬድዋን ሁሴን ፣ እነ ርዮት አለሙ የተፈቱት መንግስት ማግናኒመስ (ትልቅ) ስለሆነ ነው እያለን ነው፣ ድርጅታችውን መልአካዊ አድርጎ ለማቅረብ ሲሞከር። ሆኖም፣ የገዢውች ማንነትን፣አ አዉሬነትን አሁን በአገሪቷ ዙሪያ ሁሉ ካሉ የቶርቸር ቻምበሮች (ክፍሎች) የሚሰሙ የሰቆቃ ጩኸቶች በትልቁ እያጋለጡ ነው።


ባልሰሩትና ባልፈጸሙት ወንጀል፣ ቢያንስ ሃያ ዘጠኝ የሚሆኑ በእሥር የሚማቁ የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችን አባላት አሉ። ፍርድ ተነፍገው በፍርድ ቤት የሚጉላሉ። ፍርድ ተዛቦቶ፣ በዉሸት ምስክርና በፖለቲካ መመሪያ ጥፋተኛ ብለው፣ በቃሊቲ፣ በዝዋይ፣ በሸዋሮቢት በቂሊንጦና፣ በማእከላዊና በተለያዩ ዘግናኝ ጉላግ እሥር ቤቶች፣ ሰብዓዊ መብታቸው ተረግጦ፣ በአሁኑ ሰዓት እየተሰቃዩ ነው።

ኢትዮጵያዊያ ንጻነታችንን የምናገኝው፣ ወያኔዎች ሩህሩህ ሰለሆኑም ኦባማ ስለመጣ ሳይሆን እና በጋራ ፣ በአንድነት፣ መንቀሳቀስ ስንጨምር ነው። ትግሉ የጥቂቶች ሳይሆን የሚሊዮኖች ሲሆን ነው።

ከዚህ በታች የተዘረዝሩት አሁን በእሥር ያሉ፣ ከሚታወቁ የአንድነት ፓርቲ ወገኖቻችን መካከል የተወሰኑት ናቸው። እነዚህ ወገኖች ፍዳ የሚበሉት ለነጻነትና ለሕዝብ ነው። ሌሎቻችን የነርሱን ፈለግ ተከትለን የነጻነትና የለዉጥ ጥያቄን የበለጠ ማስተጋባት ይጠበቅብናል። እንነሳ፣ የነጻነት አርበኞች እንሁን። ግፍ፣ ጭቆና፣ ፍርሃትና ቀንበርን “በቃ” እንበል። ከሚሊዮኖች አንዱ እንሁን!!!!

1. አንዱዋለም አራጌ የአንድነት ምክትል ፕሬዘዳንት የነበረ
2. ሃብታሙ አያሌው የአንድነት የሕዝብ ግንኝነት ክፍል ሃላፊና የሚሊዮኖች ንቅናቄ ግብረ ኃይል ሰብሳቢ የነበረ
3. አለነ ማጸንቱ የአንድነት የሥራ አስፈጻሚ አባልና የማህበራዊ ጉዳይ ሃላፊ የነበረ
4. ዳንኤል ሺበሺ የአንድነት የድርጅት ጉዳይ ም/ሃላፊና የብሄራዊ ምክር ቤት አባል የነበረ
5. ስንታየሁ ቸኮል የአዲስ አበብባ አንድነት የወጣቶች ጉዳይ ሃላፊ
6. ናትናኤል መኮንን የአንድነት የብሄራዊ ምክር ቤት አባል የነበረ
7. ሃዲያ ሞሃመድ የአንድነት ፓርቲ የወላይታ ዞን አመራር የነበረች
8. ታመነ መንገሻ የአንድነት ፓርቲ የመቱ ዞን አመራር የነበረ
9. አንድዋለም አየለ ከአዲስ አበባ
10. መላኩ ተፈራ ከአዲስ አበባ
11. መሳይ ትኩ ከፍቼ
12. ቆንጨሬ ሳፋይ ከቦረና
13. ብርሃኑ ሳፋይ ከቦረና
14. በድሉ መንግስቱ ከቦረና
15. ብርሃኑ ሲሳይ ከቦረና
16. ሃብታሙ ገብረ ሚካኤል ከኮንታ
17. ምትኩ ገብረ ሚካኤል ከኮንታ
18. ጥላሁን አበበ ከጎጃም
19. ሻምበል የሺዋስ ይሁን ከጎጃም
20. አንጋው ተገኝ ከጎንደር
21. አባይ ዘዉዱ ከጎንደር
22. እንግዳው ዋኝው ከጎንደር
23. በላይነህ ሲሳይ ከጎንደር
24. አለባቸው ማሞ ከጎንደር
25. አቤል ዘለቀ ከጎንደር
26. መቶ አለቃ ሃይማኖት አያና ከጎንደር
27. ምህረት ገበየሁ ከጎንደር
28. ጸጋዬ ገበየሁ ከጎንደር
29. አሳምነው

No comments:

Post a Comment

wanted officials