Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, July 26, 2016

ሕወሓት አማራ አይደላችሁም ሲል በ13 አማሮች ላይ ክስ መሰረተ

ከሊዲያ ዘወልቃይት

የአናሳው ቡድን ትግሬ ክልል “ዐማራ ነን” ባሉ ወልቃይት ጠገዴ አማሮች ላይ ክስ መሰረተ፤ በአውሮፕላን የተጓዙበት ቲኬትም በወንጀል ማስረጃነት ቀርቧል።
የትግራይ ክልል የወልቃይት ጠገዴ የዐማራ ማንነት አስተባባሪ ኮሚቴዎችና የማኅበረሰብ አባላት ላይ የመሠረተው ክስ ዛሬ ሐምሌ 16 ቀን 2008 ዓ.ም. ይፋ ሆኗል፡፡ የትግራይ መንግሥት በ34 የወልቃይት ጠገዴ ዐማሮች ላይ የመሠረተው ክስና ማስረጃ ብሎ ያቀረበው ባለ 250 ገጽ የትግርኛ ድርሰት በግልጽ እንደሚያሳየው የወልቃይት ጠገዴ ዐማሮች ‹‹እኔ ዐማራ ነኝ›› ማለታቸው፣ የተለያየ ጊዜ ለሚመለከታቸው አካላት ማመልከቻዎችን ማስገባታቸው፤ በባንክ ገንዘብ ማንቀሳቀሳቸው ብሎም አንደኛው ተከሳሽ ከጎንደር ወደ አዲስ አበባ በአውሮፕላን መጓዙ በወንጅል ከተከሰሱባቸውን የወንጀለኛነታቸው ማስረጃ ሆነው ቀረበዋል፡፡
በምስክርነት በዳንሻና በአካባቢው በሠፈራ የመጡ ትግሬዎችና የሕወሓት አመራሮች ተዘርዝረዋል፡፡ የደደቢት ማይክሮ ፋይናንስ፣ የአንበሳና የወጋገን ባንኮች አብረው ከሳሽ ሆነው ቀርበዋል፡፡
የትግራይ መንግሥት አቃቢ ሕግ ባቀረበው ክስ መሠረት የዐማራ ማንነት የሚባል ጥያቄ እንደሌለ ደምድሟል፡፡ ይህም ለፌደሬሽን ምክር ቤት ገብቶ የፌደሬሽን ምክር ቤትም እንዲታይ ያስተላለፈውን ውሳኔ የሚጣረር ነው፡፡
ይህ ዝባዝንኬ የትግርኛ ድርሰት 254 ገጽ ሲሆን ጭብጥ ተብለው የቀረቡትን የተወሰኑ ገጾች ከትግርኛ ወደ አማርኛ መልሰን በሚከተለው መልኩ አቅርበነዋል፡፡
(ለሕግ ምኁራንና ለፖለቲካ ተንታኞች ያመች ዘንድ ወደ አማርኛ ተመልሷል)፡፡
የዐማራ ትግል ያሸንፋል!!
=================================================
ቁጥር 1207 08
ቀን 20 /10 /08
ለትግራይ ክልል ከፍተኛ ፍርድቤት ምድብ ችሎት መቀሌ
የ ት· ክ· አ·ህ·ወ·መ·ቁ————
የ ት·ክ·ከ·ፍ·ቤ·ወ·መ·ቁ———
የ ፖ·ወ·መ·ቁ———————
ከሳሽ— የትግራይ ክልል ፍትህ ቢሮ አቃቢ ሕግ
ተከሳሾች—
1. አቶ አሻግረው ገዛኸኝ ላቀው አድራሻ ወረዳ ጸገዴ ዳንሻ ከተማ ቀበሌ 01
2. አቶ አሊጋዝ አየለ አበበ ጸገዴ ወረዳ ዳንሻ ከተማ ቀበሌ 01
3. አቶ ግዛቸው ደረሰ ኃይሉ አድራሻ ጸገዴ ወረዳ ዳንሻ ከተማ ቀበሌ03
4. አቶ ሰሎሞን ግዛቴ እንየው አድራሻ ጸገዴ ወረዳ ዳንሻ ከተማ ቀበሌ 03
5. አቶ ኃይሉ አለማው ጸገዴ ወረዳ ዳንሻ ከተማ ቀበሌ 01
6. አቶ ሰጠኝ ደረስ አድማሴ አድራሻ ወረዳ ጸገዴ ከተማ ዳንሻ ቀበሌ 03
7. አቶ ሰረበ ሙሉ መሰለ አድራሻ ወረዳ ጸገዴ ከተማ ዳንሻ ቀበሌ 03
8. አቶ ጀጃው በሪሁን መልኬ አድራሻ ወረዳ ጸገዴ ከተማ ዳንሻ ቀበሌ 01
9. አቶ ሊላይ ብርሃኔ በየነ አድራሻ ወረዳ ጸገዴ ከተማ ዳንሻ ቀበሌ 01
10. አቶ ተክላይ ኃይሉ ግርማይ አድራሻ ክልል 3 ከተማ ጎንደር ቀበሌ 01 ቀጠና 03
11. አቶ እቁባይ ገ/ስላሴ ገ/ሚካኤል አድራሻ ክልል 3 ከተማ ጎንደር ቀበሌ 01 ቀጠና 03
12. አቶ ብርሃኑ መርሻ ባየ አድራሻ ክልል 3 ከተማ ጎንደር ቀበሌ 04
13. ቄስ አዱኛ ዋሲሁን ገ/እግዚአብሄር አድራሻ ወረዳ ጸገዴ ንኡስ ወረዳ ዳንሻ ቀበሌ 01
አንደኛ ክስ ከላይ ከ1 እስከ 9 የተጠቀሱት ተከሳሾች የወንጀል ዓይነት ዝርዝር ወንጀል ተከሳሾች ወንጀሉን ለመፈጸም አስበው፣ ከወርሀ ታህሳስ 2008 ዓም ጀምሮ በዳንሻ ከተማ በተለያዩ ጊዚያት ቀድሞ የተመለሰውን የማንነት ጥያቄ አሁን ያለ በማስመሰልና ሕገ መንግሥታዊ የመብት ጥያቄ ሽፋን በማድረግ ሕገ መንግሥቱን በሚቃረን መልኩ የሕዝቡን አንድነት በሚያፈርስ አኳኋን፣ ሕዝቦች እርስበርስ እንዲጋጩ በማሰብ ሕጋዊ የሕዝብ ዉክልና ሳይኖራቸው፣ ከሕግ ዉጭ የማንነት ጥያቄ አለን፤ የወልቃይት ጠገዴ መሬት ተከዜ ምላሽ ነው፤ አሁን የቆምንበት መሬት የአማራ መሬት ነው፤ ለዚህም ለሕዝብ የማንከፍለው መስዋእትነት የለም እያሉ ከሕግ ዉጭ ሕዝብን እያደራጁ፣ የተለያዩ ቀስቃሽ ጽሑፎችን ፕላምፍሌት፣ በጋዜጣ፣ በኮምፒተር ጽሑፍ እየበተኑ የቅስቀሳ ተግባር ሲፈጽሙ ቆይተዋል። ይህን ዓላማቸውን ለማሳካት ሲሉም 9ኛ ተከሳሽ እንደታፈነ አስመስለው ሕዝቡን ለአመጻ በማነሳሳት ከቀን 11/07/08ዓም እስከ ቀን 12/07/08 ዓም ሕገወጥ አመጽና አድማ በማስነሳትና በመምራት፣ ከዳንሻ ጸገዴ ጎንደር መገናኛ አስፋልት መንገድ በድንጋይ እንዲዘጋ፣ ከሁመራ ወደ ዳንሻ መናሀርያ የሚገቡ መኪኖች አስፋልት መንገዱ በድንጋይና በግንድ ዘግተው ሕዝቡ ለአመጽና አድማ እንዲነሳ በማድረግ ለ2 ቀናት የትራንስፖርት አገልግሎት ቆሞ 1824 ሰዎች የመንቀሳቀስ መብታቸዉ እንዲገደብ፣ በዳንሻ ከተማ ዉስጥ የሚገኙ የግል ተቋማት 208720 (ሁለት መቶ ስምንት ሺ ሰባት መቶ ሀያ ብር) ገቢ እንዲያጡ፣ ያንበሳ ባንክ በቀን የሚያንቀሳቅሰው ብር 3500000 – 4000000(ከሶስት ሚሊዮን አምስት መቶ ሺ እስከ አራት ሚሊዮን ብር)በሁለት ቀናት አመጽ ከ7000000−8000000 ብር (ከሰባት እስከ ስምንት ሚልዮን ብር፣ ወጋገን ባንክ በቀን የሚያንቀሳቅሰው ብር 600000(ስድስት መቶ ሺ ብር) በሁለት ቀናት አድማ ዉስጥ (1200000 አንድ ሚልዮን ሁለት መቶ ሺ ብር ፣ ደደቢት ማይክሮ ፋይናንስ በቀን የሚያንቀሳቅሰው ገቢ ብር 1493977 (አንድ ሚልዮን አራት መቶ ዘጠና ሶስት ሺ ስድስት መቶ አስራ ሁለት ብር) እንቅስቃሴው እንዲቆም፣ መንግሥታዊ ጽፈት ቤቶች እንዲዘጉ፣ እንዲሁም በአቶ ገ/ጨርቆስና መኮነን ተክላይ ንብረት ላይ 5100 ብር የሚገመት ጉዳት እንዲደርስ በመምራትና በማንቀሳቀስ በፈጸሙት የሕዝብ አንድነት የመንካት ወንጀል ተከሰዋል።
ሁለተኛ ክስ ከ1 እስከ 9 ያሉ ተከሳሾች የወንጀል ዓይነት የኢፈድሪ ወንጀል መቅጫ ሕግ አንቀጽ 32(1− ሀ−ለ)257/ሀ/ የተደነገገዉን በመተላለፍ መገፋፋትና ግዙፍ የሆነ የመሰናዳት ተግባር ወንጀል ወልቃይት ጠገዴ የትግራይ አካል ሳይሆን አማራ ነው፤ ትግሬዎች የምንፈልገው መሬታቹን እንጂ እናንተን አደለም እያሉን ነው። ወልቃይት ጸገዴ ቋንቋውን ባህሉን እንዳያሳድግ ተከልክሎሏል እያሉ ትክክለኛ ያልሆነና ጥላቻ የተሞላ የሕዝብ አቋም በሚያፈርስ መልኩ በተለያዩ ሕዝባዊ መድረኮች በመናገር ይንቀሳቀሱ ስለነበር በፈጸሙት ወንጀል ተከሰዋል።
ሶስተኛ ክስ ከ1 እስከ 8 ያሉት ተከሳሾች የወንጀል ዓይነት የኢፈድሪ ወንጀል መቅጫ ሕግ አንቀጽ 32(1−ሀ) 490(3) የተደነገገዉን በመተላለፍ ሕዝባዊ ስብሰባን በማወክ ተከሳሾች በወርሀ ታህሳስ 2008 ዓም በግምት 2∶30 አከባቢዳንሻ ከተማ ልዩ ቦታ ማዛጋጃ ቤት በነበረውን የወጣቶች መልካም አስተዳደር ስብሰባ ይመራ ለነበረ ጠዓመ ለምለም የመልካም አስተዳደር ችግር አለብን፤ ስልጣን አልተሰጠንም፤ የእርሻ መሬትና የመኖሪያ መሬት አልተሰጠንም፤ ስለዚህ አንተ ልትመራን አትችልም ዉጣልን ብለው በማወክ ስብሰባው እንዲበተን በማድረግ በፈጸሙት ወንጀል ተከሰዋል።
አራተኛ ክስ ከ1−8 ያሉት ተከሳሾች የወንጀል ዓይነት የኢፈድሪ ወንጀል መቅጫ ሕግ አንቀጽ 32(1−ሀ)490(3)የተደነገገውን በመተላለፍ ሕዝባዊ ስብሰባን በማወክ ወንጀል ግደይ አዛናው ለታባለ ስብሰባ ይመራ ለነበረ የጸገዴ አስተዳዳሪ አንተ ስብሰባዉን ልትመራው አትችልም ማንነታችን አማራዎች ነን በማለት ስብሰባዉን በማወክ ወንጀል ተከሰዋል።
አምስተኛ ክስ ከ1−8 ባሉ ተከሳሾች ላይ የወንጀል ዓይነት የኢፈድሪ ወንጀል መቅጫ ሕግ አንቀጽ 32(1−ሀ) 441(1−ሀ) የተደነገገውን በመተላለፍ የመንግሥት ሥራዎችን በማደናቀፍ ወንጀል ተከሳሾች የካቲት 2008 ላይ ጎይትኦም ርስቀይ የተባለ ታሳሪ ታስሮ እያለ ከዳንሻ ከተማ ፖሊስ ጽ/ት ቤት 80 ሰዎችን ሰብስበው ጎይትኦም ለምን ይታሰራል? የማንነት ጥያቄዉን በመጠየቁ ለምን ይታሰራል? አሁንኑ ይፈታልን በማለት ፖሊስ ስራውን ባግባቡ እንዳይሰራ በማስፈራራት ወንጀል ተከሰዋል።
ክስ ስድስት ከ1−9 ባሉት ተከሳሾች ላይ የወንጀል ዓይነት በኢፈድሪ ወንጀል ሕግ አንቀጽ 32(1−ሀ/ለ/38/1/506(1−ለ) የተደነገገውን በመተላለፍ በመኪኖች ላይና መተላለፊያ መንገድ መሰናክል የመፍጠር ወንጀል ተከሳሾች ከ ቀን 11/07/2008ዓም እስከ ቀን 12/07/2008ዓም ከቀኑ 7∶00 ሲሆን በጸገዴ ወረዳ ንኡስ ወረዳ ዳንሻ ወደ ወደ ጎንደር መሄጃ መንገድ በድንጋይና በግንድ በመዝጋት፣ ከሁመራ ወደ ዳንሻ መናሃሪያ የሚገቡ መኪኖችን በመዝጋት ሕዝባዊ አመጽ በማስነሳት ለ2 ቀናት የትራንስፖርት እንቅስቃሴ በማስቆም ወደ 1,824 ገደማ ሰዎች የመንቀሳቀስ መብታቸውን በማገድ ይመሩና ያንቀሳቅሱ ስለነበር፣ በዚህ ተከሰዋል።
ሰባተኛ ክስ በ8ኛ ተከሳሽ ላይ የወንጀል ዓይነት የኢፈድሪ ወንጀል ሕግ አንቀጽ 32(1−ሀ)486(ለ)የተደነገገውን በመተላለፍ የዉሸት ወሬ በመንዛት ሕዝብ እንዲነሳሳ የማድረግ ወንጀል ተከሳሽ በቀን 19/06/08 ዓም በግምት ከምሽቱ 2 ሰአት ሲሆን ልጃቸው በስራ ጉዳይ ወደ ጎንደር እየሄደ እያለ በዳንሻ ከተማ ልዩ ስሙ የወይዘሮ ጸጋዬ መከታ ቡና ቤት በመሄድ ልጅሽ አለኸኝ አቻምየለህ በፖሊስ ታፍኖ ተወሰደ ብሎ የዉሸት ወሬ በመንዛት በመንግሥት አካላት ላይ ጥርጣሬ በማስፋፋት በሰራው ወንጀል ተከሷል።
ስምንተኛ ክስ በ10ኛ−13ኛ ላይ የወንጀል ዓይነት የኢፈድሪ ወንጀል ሕግ አንቀጽ 32(1−ሀ)486(ለ) የተደነገገውን በመተላለፍ የዉሸት ወሬ በመንዛት ሕዝብ እንዲነሳሳ ማድረግ ወንጀል ተከሳሾች በቀን 09/07/08ዓም እስከ 10/07/08አም ባሉት ቀናት ሊላይ ብርሃኔ አመጽ ለማነሳሳት ሆን ብሎ ወደ ሌላ ቦታ ሄዶ እያለ ከጎንደር ወደ ዳንሻ ሲመጣ በመንግሥት የድህንነት አካላት ታፍኖ ብለው የዉሸት ወሬ በመንዛት፣ በጸገዴ ወረዳ የሞተ አማራ ሰው አለ ብለው ትግሬንና አማራን ለማጣላት በፈጸሙት ወንጀል ተከሰዋል።
ማስረጃ(ምስክር)
ሀ የሰው ምስክር
1. አቶ ጠዓመ ለምለም አድራሻ ወረዳ ጸገዴ ንኡስ ወረዳ ዳንሻ ቀጠና 02
2. ሳጅን ብርሃነ አማኑኤል ወላይ >> >> >> >> >> >> >> >> 02 3
3. አቶ ተከስተ ገ/ሊባኖስ ደሞዝ >> >> >> >> >> >> >> >> 01
4. ሳጅን ጸጋይ ፍስሃ አብርሃ >> >> >> >> >> >> >> >> 02
5. ወ/ሪት ሓዳስ አማረ አብርሃ >> >> >> >> >> >> >> >> 02
6. ሳጅን አሸብር ሲሳይ ትርፌ >> >> >> >> >> >> >> >> 02
7. አቶ ሹሙዬ አለምነህ ወንድምአገኝ >> >> >> >> >> >> >> >> 02
8. አቶ ገዳሙ ድራር ኪ/ማርያም >> >> >> >> >> >> >> 03
9. አቶ ሃይለ ሃያል ተስፋይ >> >> >> >> >> >> >> >> 02
10. ሻምበል እሸቴ አወቀ ምትኬ >> >> >> >> >> >> >> >> 04
11. መ/ሃለቃ አበራ አዱኛ >> >> >> >> >> >> >> >> 01
12. አቶ ሽሀይ ደመቀ ተስፋይ >> >> >> >> >> >> >> >> 02
13. አቶ ወላይ ገብሩ ለምለም >> >> >> >> >> >> >> >> 04
14. አቶ ጫኔ እንዴትላርግህ አበራ >> >> >> >> >> >> >> >> ማይደሌ
15. ወ/ሮ ጸጋዬ መከተ እንዴትላርግህ >> >> >> >> >> >> >> >> 04
16. አቶ ደመቀ እያሱ እሸቴ >> >> >> >> >> >> >> >> 03
17. አቶ ዳዊት ካሰየ ሃብቱ >> >> >> >> >> >> >> >> 03
18. አቶ ስማቸው ካሳሁን ገ/ጊዮርጊስ >> >> >> >> >> >> >> >> 04
19. አቶ አለኸኝ አቻምየለህ እሸቴ >> >> >> >> >> >> >> >> 04
20. አቶ መኩሪያ ሸተይ ለምለም >> >> >> >> >> >> >> >> 01
21. አቶ ግዛቸው ብርሃነ በየነ >> >> >> >> >> >> >> >> 04
22. አምሳ አለቃ ርጥበይ በየነ ደስታ >> >> >> >> >> >> >> >> 01
23. አቶ ገብረ ሰረበ ሳሙኤል >> >> >> >> >> >> >> >> 01
24. አቶ ደመቀ ጸጋየ አለማዮሁ >> >> >> >> >> >> >> >> ማይደሌ
25. አቶ ብርሃነ በየነ ደስታ >> >> >> >> >> >> >> >> 04
26. አቶ ጀጃው ይርጋ ከፍያለው >> >> >> >> >> >> >> >> ማይደሌ
27. አቶ ኪዳነ ግርማይ ገ/ማርያም >> >> >> >> >> >> >> >> 02
28. አቶ ሃፍቶም ገሰሰው ተገኘ >> >> >> >> >> >> >> >> 03
29. ተማሪ ዳኛቸው አንጋው ተስፋይ >> >> >> >> >> >> >> >> 03
30. አቶ ከፍያለው ሃይሉ ገ/እግዚአብሄር >> >> >> >> >> >> >> >> 02
31. አቶ ደሳለኝ ወልዱ ደጉ >> >> >> >> >> >> >> >> 04
32. አቶ ጎይትኦም መኩሪያ ገ/ማርያም >> >> >> >> >> >> >> >> 01
33. አቶ ብርሃነ ገ/ጨርቆስ ደሞዝ >> >> >> >> >> >> >> >> 04
34. አቶ መኮነን ተክላይ ገ/ማርያም >> >> >> >> >> >> >> >> 04
የጽሑፍ ማስረጃ (ምስክር)
በቀን 20/5/2008 ዓ/ም 32 የሚሆኑ ሰዎች የፈረሙበት ይታወቅልን የሚል ወደ ን/ወ/ዳ አስተዳደር የተጻፈ 2 ገጽ ደብዳቤ 2 ሕገ መንገስታችንና የወልቃይት ጠገዴ በደል ይነጻጸር እያለ ስለ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 29፣30፣39 እና 46 የተጻፈ ትንተና ከትግርኛ ትርጉሙ ጋር 5 ገጽ 3 የወልቃይት ሕዝብ የአማራ ብሄርተኝነት የማንነት ጥያቄ አመለካከት የሚል ጽሑፍ ከትግርኛ ትርጉሙ ጋር 15 ገጽ 4 የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ሆይ ከእንቅልፍህ ንቃ የሚል አነሳሽ ግጥም ከትግርኛ ትርግሙ ጋር 4 ገጽ 5 የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ንቃ ሳይደበዝዝ የሚል በግልጽ ትግሬዎች ወልቃይት ጠገዴ መሬቱን እንጂ ሕዝቡን አንፈልገውም እያሉ እንዴት ከነሱ ጋር አብረን እንኖራለን የሚል አነሳሽ ጽሑፍ ከትግርኛ ትርጉሙ ጋር 2 ገጽ 6 የጠገዴ ሕዝብ ሆይ ድል ለእውነተኞቹ ውርደት ለውሸታሞቹ የሚል አነሳሽ ጽሑፍ ከትግርኛ ትርጉሙ ጋር 6 ገጽ 7 ሊላይ ብርሃኔ ከጎንደር አዲስ አበባ በመጋቢት 19/2016 የተጓዘበት የፕሌን ቲኬት ከኦሪጂናሉ ጋር 3 ገጽ 8 አቶ ብርሃኔ በየነ (የሊላይ አባት) በቀን 11/07/2008 ዓ/ም ልጄ ጠፋብኝ ብሎ ለጠገዴ ወረዳ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ያስገቡት ማመልከቻ 1 ገጽ 9 ተጠርጣሪ ሊላይ ብርሃኔ በፋ/መ/ቁ 761 በቀን 26/07/2008 ዓ/ም በትግራይ ምእራባዊ ዞን መካከለኛ ፍርድ ቤት 10 አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ በቀን 20/07/2008 ዓ/ም በቁጥር አ/ኢ/ባ/ደቅ/395/08 የሰረበ ሙሉ፣አሊጋዝ አየለ፣ ሞላ ኃይሉ፣ ጀጃው በሪሁን፣ ወንድይፍራው አታላይና አሻገረው ገዛኸኝ የባንክ እንቅስቃሴ (Bank statement) የሚገልጽ ጽሑፍ ከትግርኛ ትርግሙ ጋር 20 ገጽ 11 በሕገ ወጥ ሽብርና ሰልፍ ምክንያት በወጋገን ባንክ ላይ መሰራት የነበረበት ስራ ባለመሰራቱ የሚል ጽሑፍ በቁጥር ወ/ደ/ቅ/7/41/7 በቀን 23/7/2008 ዓ/ም የተጻፈ ደብዳቤ ከትግርኛ ትርግሙ ጋር 2 ገጽ ማስረጃ 12 በቀን 11/07/2008 ዓ/ም በተካሄደው ሕገ ወጥ ሽብርና ሰልፍ ምክንያት አንበሳ ባንክ ላይ መሰራት የነበረበት ያልተሰራ ስራ የሚል በቁጥር አ/ኢ/ባ/ዳት397/08 በቀን 21/07/2008 ዓ/ም የተጻፈ ደብዳቤ ከትግርኛ ትርግሙ ጋር 2 ገጽ ማስረጃ 13 በጠገዴ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ጥናት ሽያጭ የሚካሄድባቸ ዘርፎች ብዛት የሚያሳይ በቁጥር በቁጥር ጠ/ወ/ገ/2112/38/ካ በቀን 22/7/2008 የተጻፈ 2 ገጽ ማስረጃ 14 በቀን 11/7/08 ዓ/ም በነበረው ሽብር መንቀሳቀስ የነበረባቸው ሳይንቀሳቀሱ የቀሩ የመኪናና የሰው ብዛት የደረሰው ኪሳራ የሚገልጽ በቁጥር ከ/መ/ኑ/4504/25/2 በቀን 22/07/2008 ዓ/ም ከጸገዴ ኮ/መ/ትራንስፖርት ጽ/ቤት የተጻፈ 1 ገጽ ማስረጃ 15 በቀን 11/07/08 በነበረው ሽብር ምክንያት እንደተዘጋና መንቀሳቀስ የነበረበት ገንዘብ 16 17 የ 61 ሰዎች ስም ዝርዝርና ፊርማቸውና ስልካቸው የያዘ 2 ገጽ ማስረጃ 18 የ 21 ስም ዝርዝር፣ አድራሻቸው፣ ስልካቸውና ፊርማቸው የያዘ 1 ገጽ ማስረጃ ቁጥር 1207 08 ቀን 20 10 08

No comments:

Post a Comment

wanted officials