Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Saturday, July 30, 2016

የረኀብ አድማ ከመቱ 9ኛ ቀናቸውን ያስቆጠሩት 9 የፖለቲካ እስረኞች ራሳቸውን ስተው በግሉኮስ መሆናቸውን ቤተሰቦቻቸው ለኢሳት ገለጹ






ኢሳት ሰበር ዜና

የረኀብ አድማ ከመቱ 9ኛ ቀናቸውን ያስቆጠሩት 9 የፖለቲካ እስረኞች ራሳቸውን ስተው በግሉኮስ መሆናቸውን ቤተሰቦቻቸው ለኢሳት ገለጹ።
ከኃምሌ 13 ጀምሮ ከቤተሰቦቻቸው የሚሄድላቸውን ምግብ ያልተቀበሉ ሲሆን፣ በትላንትናው ዕለት እና ከትላንት በስቲያ ሰውነታችው ደክሞ በአምቡላንስ ወደ ሆስፒታል የተወሰዱ እንዳሉ ለመረዳት ተችሏል።


1.በቀለ ገርባ 2.ብርሀኑ ተክለያሬድ 3.ዮናታን ተስፋዬ
4.ደጀኔ ጣፋ 5.ፍቅረማርያም አስማማው 6.ማስረሻ ሰጠኝ
7.ጉርሜሳ አያኖ 8.አዲሱ ቡላላ 9.አበበ ኡርጌሳ

ከላይ የተዘረዘሩት የፖለቲካ እስረኞች 5 ነጥብ ያለው መግለጫ አውጥተው የምግብ ማቆም አድማ መጀመራቸው ይታወሳል።
1. በሽብርተኛነት ተከሰው በእስር ቤት ያሉ እስረኞች ላይ የሚፈጸመው አሰቃቂ ምርመራ እንዲቆም
2.ፍርድ ቤቶች ነጻ ካለመሆናቸው የተነሳ ፍርድ ያጓትታሉ፣ በክልል መታየት የሚገባቸውን ጉዳዮች ያለሕግ በመንጠቅ ወደፌደራል ፍርድቤቶች መውሰድ ፌዴሬሽኑን የማፍረስ ተግባር ስለሆነ በአስቸኳይ እንዲቆም።
3.በፖለቲካ አመለካከታቸው ብቻ ለእስር ተዳርገው የሚገኙ ዜዜጎች ላይ የሚፈጸመው ግፍ እና አድልዎ ይቁም
4.በተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች ተሰማርቶ እየገደለ ሰቆቃ እየፈጸመ የሚገኘው የፌደራል ሠራዊት እንዲወጣ እና በዜጎች ላይ የሚፈጸመ አፈና፣ እስራት፣ ግድያ እንዲቆም
5. ሕገወጥ በሚል ሰበብ በዚህ ክረምት የዜጎችን ቤት የማፍረስ ድርጊት በአስቸኳይ እንዲቆም
ይህን እየጠየቅን በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር የሚገኝ ሕዝባችን ስለሰብአዊ መብት መከበር እና ስለፍትሕ ከጎናችን እንዲቆም ጥሪ እናቀርባለን::

No comments:

Post a Comment

wanted officials