Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Wednesday, July 20, 2016

የኢትዮጵያ ኦሎምቲክ ኮሚቴ ለህውሃት ሚሊየን ብሮችን አስረከበ



2016-07-16-02-33-17--1818555830
ቶማስ ሰብስቤ
ለዘንድሮ ብራዚል  ኦሎምፒክ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ የገቢ ማሰባሰቢያውን እያገባደደ ነው።ጨርሷልም የሚሉ አሉ።በዚህ የማሰባሰቢያ የተገኘው ገቢ ሁለተኛ ከፍተኛ በጀት ግን ወደ ህውሃት ንብረት ዋፋ ነው የሚገባው።
ዋፋ ስንት ብር ያገኛል――ለምን?
ዋፋ የማስታወቂያ እና የገቢ ማሰባሰቢያው በበላይነት ሰለሚሰራ ቢያንስ 15 ሚሊየን ብር ተሰቶታል ተብሏል።ይህን ሰሰማ በወንዶች 10 ሺ እንደው ደከም ሰላልን ዋፋ በዚህ ርቀት ሊሮጥ ይሆን ብያለው።
ጨረታ የሌለው አሸናፊነት!
ማንም አልተወዳደረም ሳይሆን ስራው ያለቀው በቤተሰብ ዋጋ ነው።ምክንያት ካላችሁኝ በፌደራል ወጣቶች እና ሰፖርት ሚኒስቴር ውስጠ ደንብ ላይ እንዲ ይላል «የትኛውም መንግስት የሚሰራቸው የገቢ ማሰባሰቢያ በዋፋ በኩል ይፈፀማል»።ታዲያ ይህ ህግ ካለ ጨረታ ጆከር ነው ብል ምን ያነሰኛል።
ዋፋ እንዴት የህውሃት ልጅ ሆነ የምትሉ ?
ዋፋ ማለት እንደ ቁምሳ ነው።በቀን ሶሰቴ መብላት ያልቻልነው ኢትዮጵያዊያነን  በአንድ ወቅት በዚህ ቀመር በልተናል።ቁርስ አምስት ሰዓት ፣እራት  አስራ አንድ ሰዓት።ለዚም ከቁርስ,,,,,,ቁ ፣ ከምሳ,,,,, ምሳ ወስዶ ቁምሳ እንዳለው በእውቀቱ።ዋፋ እንደዛው ነው። ዋልታ እና ፋና አንዳንድ ፊደል አዋተው ነው።በእናትም በአባትም አንድ ሆንው ዋፋ ያሉት።ከግራ ኪስ ቀኝ ኪስ ማለት ይሄ ነው።እዚህ ላይ ምርመራ ጋዜጠኝነት ሰራለው ብትል አሸባሪ ነህ።
የዋፋን  ጠበቃ ማነው?
እውነት ለመናገር ዋፋ ይህን ብር ሳያውቀዉ በአራት አመት አንዴ የሚመጣለት ህውሃት ጠይቆ ሳይሆን በ ፖለቲካ ሂሳብ ነው።የኦሎምፒክ ኮሚቴው በህውሃት እና ኦፒዲዮ  ስራ አስኪያጆች ይመራል።ሲዝናኑ እንኳን ከዋካ ዋካ ይልቅ ዋፋ ይመጣባቸዋል።
ዘንድሮስ እንደ ለንደን ከአትሌቶቹ በላይ ኮሚቴ ይበዛል ለመሄድ!
አይ ! ይህ እማ ብራዚል እኮ ነው አይበዙም ካላቹ ተሳስታችሃል።ጫወታው የቀን አበል ፤ ጥቅማ ጥቅም ነው።ሮጦ ወርቅ ከሚያመጣው ቁጭ ብሎ የሚያጨበጭ ኮሚቴ አበሉ ይበዛል።ደሞ ሲመጡ የሚሸጥ እቃ ያመጣሉ እና ሜዳሊያ እንዳይረሳ።
የመጀመሪያው የመንግስት ድጋፍ ውሃ እንዳይበላው!
በኦሎምቲክ ታሪክ ለሀገራችን ኮሚቴ መንግስት ድጋፍ አድርጓል ዘንድሮ።ልክ እንደ ኬንያ መድቡልን ብላቹ በዛው ከውጤቱ ጋር እንዳይጠፋ መጠንቀቅ።የታቀደው 4 ወርቅ ፣4 ብር ፣ 4 ነሃስ ሜዳሊያ ብዙ ሰራ ይሻል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials