Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, July 12, 2016

የቅማንት ጥያቄ፤ የአፈታቱ ፈተናና ከጥያቄው ጀርባ የተደበቁ ሰዎች ማንነት – አለሙ ይግለጤ

እንደ መቅድም
tplf_PAFDየኢህአዴግ መንግስት አገራችንን በዘጠኝ ብሄር ተኮር ክልሎችና ሁለት የከተማ አስተዳደሮች እንዲዋቀር የሚደነግግ ሕገመንግስት በ1987 ዓ.ም አጸደቀ። በዚህ ሕገመንግስት መሰረት ከተቋቋሙት የብሄር ብሄረሰብ ክልሎች መካከል አንዱ የአማራ ብሔራዊ ክልል ነው። የአማራ ብሔራዊ ክልል በዋነኛነት የአማራ ህዝብ የሚኖርበት ክልል ሲሆን በውስጡ የአዊ፣ ህምራ፣ ኦሮሞ፣ አርጎባ፣ ቅማንትና የሌሎችም ብሄረሰቦች ተወላጆች የሚኖሩበት ክልል ነው። የአዊ፣ ህምራና ኦሮሞ ብሄረሰቦች የክልሉ መስተዳድር ሲመሰረት ጀምሮ በክልሉ ህገመንግስት መሰረት በዞን ደረጃ የብሄረሰብ ም/ቤት እንዲያቋቁሙና የራሳቸው የሆነ አስተዳደር እንዲመሰርቱ ተደርጓል። የአርጎባ ብሄረሰብም በሂደት የብሄረሰቡ ልዩ ወረዳ እንዲቋቋም በክልሉ ም/ቤት በአዋጅ ከጸደቀለት በኋላ የብሄረሰቡን ም/ቤት መስርቶ እርሱን በራሱ እያስተዳደረ ይገኛል። የቅማንት ብሄረሰብ የማንነትና የራስ አስተዳደር ጥያቄም ከብዙ ውጣውረድ በኋላ ሐምሌ 2007 ዓ.ም በክልሉ ም/ቤትና መንግስት ይሁንታን አግኝቶ የብሄረሰቡ የልዩ ወረዳ ማቋቋሚያ አዋጅና የአፈጻጸም መመሪያ እንደወጣለትና የፌደሬሽን ም/ቤትም የክልሉን ም/ቤት ወሳኔ እንደተቀበለው ይታወቃል። ይሁንና በክልሉ ም/ቤትና በፌደሬሽን ም/ቢት የጸደቀው የቅማንት ብሄረሰባዊ ም/ቤትን በልዩ ወረዳ ደረጃ የማቋቋም ስራው መሬት ላይ እስካሁን አልተጠናቀቀም።
የጥያቄው አነሳስና አካሄዱ ስለመጠለፉ
ብሄረሰባዊ ም/ቤቱን የማቋቋም ስራው እንዳይከናወን ካደረጉት ምክንያቶች ውስጥ አንዱና ዋነኛው እራሱን በራሱ የቅማንት ህዝብ ተወካይ አድርጎ የሰየመ ስልጣንና ጥቅም ናፋቂ የሆነ ጠባብና አክራሪ ኮሚቴ አባላት በየደረጃው የሚያሰራጩት አፍራሽ ፕሮፖጋንዳ ተጠቃሽ ነው። እነዚህ ጠባብ ሀይሎች ቅማንቱን ከቅማንቱ እንዲሁም ቅማንቱን ከአማራው ለመለያየትና ለማዳማት ቀን ከሌት ይጥራሉ። ባለፈው በተካሄደው የህዝብና ቤት ቆጠራ ክንዉን የቅማንት ብሄረሰብ በክልሉ እንደሌለ መደረጉ ሁሉንም እኩል ያስቆጣ ድርጊት ነበር። በዚህ ቆጠራ ወቅት ሁለት ሚልዮን የአማራ ህዝብም “ባልታወቀ” ምክንያት መጥፋቱን ልብ ይሏል። የብሄረሰቡን ከክልሉ መዝገብ አለመካተት ተከትሎ ብሄረሰባዊ ማንነታችን ይታወቅ፤ የራስ በራስ ማስተዳደር መብታችን ይረጋገጥ የሚል የመብት ጥያቄ ተነሳ። የተነሳውን የመብት ጥያቄ አግባብነት በማመን ቅማንቱም አማራውም በመተባበር በአንድነት ጥያቄው በአግባቡ እንዲመለስ የሚቻለውን ሁሉ አድርጓል። ይሁንና በጥያቄው አቀራረብና አፈታት ሂደት የህዝቡን አግባብ ያለው ጥያቄ ለራሳቸው የግል መበልጸጊያና የስልጣን መወጣጫ ለማድረግ አልመው የሚንቀሳቀሱ የኮሚቴ አባላትና ደጋፊወች አልነበሩም ማለት አይደለም። በወቅቱ አንዳንድ የኮሚቴ አባላት በቅማንት ህዝብ ስም ያካሂዱት የነበረው ዘረኝነት የተሞላበት አካሄድ በተለይ ደግሞ በጋብቻ፣ በሀይማኖት፣ በባህልና አብሮ በማደግ ተሳስሮ በኖረው ወንድም የአማራ ህዝብ ላይ ያነጣጠረ ነበር። አፍራሽ የዘረኝነት ቅስቀሳቸው የሁለቱንም ወንድማማች ህዝብ አብሮነት የሚያደፈርስ፤ ለግጭትና ለግድያ የሚጋብዝ ነበር። ይህን የተገነዘቡና መጭውን አርቀው ማየት የቻሉ የሁሉም ወገኖች የጉዳዩን አሳሳቢነት በመገንዘብ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ የኮሚቴ አባላት ነን ለሚሉት ወገኖች ቆመው እንዲያስቡበት ያለመታከት ጥሪ አቅርበዋል። አክራሪ የኮሚቲው አባላት ልባቸው በመደፈኑና የሽማግሌዎችን ጥሪ ባለመቀበላቸው በኋላ ላይ የተፈራው ደረሰ። በመተማ፣ በአይከል፣ ማውራ፣ ትክል ድንጋይ ወዘተ በህዝቡ በንብረቱና በህይወቱ ላይ ከፍተኛ የሆነ ውድመት ደረሰ። የደረሰውን ውድመትም ተከትሎ የአክራሪው ኮሚቴ አባላትም የተወሰኑት ለእስራት ተዳረጉ፤ የተወሰኑት እራሳቸውን ደበቁ፤ የተወሰኑት ከኮሚቴው ስራ ራሳቸውን አገለሉ። አንዳንድ ዘረኛ የኮሚቴው አባላት ግን ውስጥ ለውስጥ እየተሽሎከለኩ አሁንም ህዝቡን በመካፋፈል ድርጊታቸው እንደቀጠሉበት ይገኛሉ።
የጥያቄው ምላሽ ማግኘት መገለጫዎች
ከላይ ለመግለጽ እንደተሞከረው በአማራ ክልልም ሆነ በፌደሬሽን ም/ቤቶች (በብአዴንም ሆነ በኢህአዴግ) እነዚህ የኮሚቴ አባላት አለን ያሉትን የቅማንት የማንነትና የራስ አስተዳደር ጥያቄ መልሰውላቸዋል። በዚህም መሰረት፦
  1. በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ውስጥ የሚገኘው የቅማንት ብሄረሰብ በአገራችን ኢትዮጵያ ከሚገኙት የተለያዩ ብሄረሰቦች ውስጥ አንዱ እንደሆነ በክልልም በአገርአቀፍ ደረጃም እውቅና አግኝቷል። በመሆኑም በክልሉና በፌደሬሽን ም/ቤት የብሄረሰቡ ተወካይ እንዲኖረው ተደርጓል። በተጨማሪም ዘንድሮ ጋምቤላ ላይ በተካሄደው ዓመታዊ “የብሄር ብሄረሰቦች ቀን” ቅማንት እንደ ብሄረሰብ ተወካዮችን በመላክ ተሳትፏል። ይህ የማንነት ጥያቄው ስለመመለሱ አስረጅ ነው።
  2. የቅማንት ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ ም/ቤት እንዲቋቋም የሚደነግግ አዋጅ የአማራ ክልል ም/ቤት በሐምሌ 2007 ዓ.ም ባካሄደው ጉባኤ አጽድቋል። የፌደሬሽን ም/ቤትም የክልሉን ውሳኔ ተቀብሎታል። በአዋጅ እንዲቋቋም በጸደቀው 42 የቅማንት ቀበሌወችን በሚያካተው ልዮ ወረዳ የቅማንት ብሄረሰብ እርሱን በርሱ እንዲያስተዳድር ተደንግጓል፤ የአፈጻጸም ዝርዝር መመርያ ተዘጋጅቶለታል። ይህ ሂደት የራስ አስተዳደር ጥያቄውን ይመልሳል።
ይሁንና አንዳንድ የኮሚቴው አባላት አሁንም የመጀመርያው ጥያቄያቸው እንዳልተፈታ በማስመሰል ህዝብን የሚከፋፍልና ለበለጠ እልቂት የሚዳርግ ቅስቀሳ ከማድረግ አልተቆጠቡም። የቀረበው የማንነትና የራስ አስተዳደር ጥያቄ እንደተመለሰ ከላይ ተገልጿል። የኮሚቴው አባላት ጥያቄያችን አልተመለሰም ማለታቸው የተደበቀ ሌላ አጀንዳ እንዳላቸው የሚያስረዳ ይሆናል።
ከጥያቄው ጀርባ የታሰበው ሴራ
የክልሉንም ሆነ የፌደራል መንግስት ውሳኔ ለመቃወም በጠባብ የኮሚቴው አባላት የሚቀርበው ሽፋን ቅማንት ከወገራ እስከ ቋራ በ8 ወረዳወች በሚገኙ 126 ቀበሌዎች ስለሚኖር ከወገራ ጀምሮ እስከ ቋራ ያለው አገር በሙሉ የቅማንት ክልል ብቻ ሆኖ ሊቋቋም ይገባል የሚል የልምዣት ነው። እነሱ አሳነሱት እንጅ ቅማንትና አማራ በሁሉም የጎንደር ወረዳዎች ሊባል በሚችል ደረጃ ተቀላቅለውና ተዋህደው የሚኖሩ ናቸው። ከዚህም የተነሳ ሁለቱ ህዝብ ይለያይ ቢባል በህዝቡ መካከል የሚያስከትለው ችግር በጣም አሳሳቢ ነው። ምን አልባትም በመተማ፣ በአይከል፣ በማውራና በትክል ድንጋይ ከታየው የበለጠ አደጋ መፈጠሩ አይቀሬ ይሆናል። ለዚህም ይመስላል ከህዝቡ ጋር በየደረጃው ብዙ ውይይት ከተደረገና ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት ጥናትም ካስጠና በኋላ የክልሉ ም/ቤት ቅማንቶች በተለይ የሚኖሩባቸው በኩታገጠምነት የተያያዙት 42 ቀበሌዎች በልዩ ወረዳ ይደራጁ ወደሚለው ውሳኔ የደረሰው። የመንግስት አካላት በተለያየ ጊዜ ከህዝብ ጋር ባደረጓቸው ውይይቶችም እንደተገለጸው ጥናቱ ወደፊትም የሚቀጥል ሲሆን ከ42 ቀበሌዎች በተጨማሪም ወደፊት መመዘኛውን የሚያሟሉ ቀበሌዎች በህዝብ ይሁንታ ሲያገኙ እየተካተቱ እንደሚሄዱ በተደጋጋሚ ተገልጿል። ይሁንና በአካባቢው መረጋጋት ሰፍኖ ህዝቡም በሰላም ወደእለት ስራው ከተመለሰ አክራሪው የኮሚቴው አባላት የግል ጥቅማቸውና በተላላኪነት የቆሙለት ዓላማ ግቡን ስለማይመታ ጭቁኑን አርሶአደርና ወጣት ተማሪዎችን መሰላል አድርገው ሊጠቀሙባችው እየሞከሩ ነው።
አክራሪ የኮሚቴ አባላቱ አርሶ አደሩን 126 ቀበሌዎችን በቅማንት ዞን ካደራጀን የቋራንና የመተማን ጥቁር አፈር መሬት ሌላውን (አማራውን ማለታቸው ነው) እያስወጣን እንሰጥሃለን እያሉ በመቀስቀስ ህዝቡን ለበለጠ እልቂት እያዘጋጁት ይገኛሉ። ለወጣት “ምሁራን” እና ተማሪዎችም በ126 ቀበሌዎች የራሳችን ዞን ስንመሰርት ለተለያዪ መምርያዎች ብዙ የተማረ ሰው ስለሚያስፈልግ አሁን ከእኛ ጋር ከተባበራችሁ ዞን ስንመሰርት ደህና ስልጣን ታገኛላችሁ፤ የዞናችን ዋና ከተማ ጎንደር ከተማ ስለሚሆን ለመኖርያና ለንግድ የሚሆን ቦታ ታገኛላችሁ ወዘተ የሚል ማማለያ በማቅረብ የጥፋት ተባባሪ ሊያደርጓቸው እየጣሩ ነው።
በአጠቃላይ ከወገራ እስከ ቋራ ያሉ የ126 ቀበሌዎች የዞን ምስረታ እና ጎንደር ከተማ የቅማንት ዋና ከተማነት ትርክታቸው የአክራሪው ኮሚቴ አባላት ጥያቄ ፊት ለፊት እንደሚሉት የማንነትና የራስ አስተዳደር ጥያቄ ሳይሆን ህዝቡን የመበታተንና የማጫረስ እንዲሁም ድብቅ ግዛት የማስፋፋት ጥያቄ መሆኑ እየተገለጠ ነው። ይህ ካልሆነ አሁን ባለው የጎንደር ከተማ አስተዳደር በሚሰጠው አገልግሎት ቅማንት ቅማንት በመሆኑ ብቻ ያጣው ምንድን ነው? አማራስ አማራ በመሆኑ ብቻ ያገኘው ምንድን ነው? ባለፉት 25 ዓመታት ውስጥ ብቻ እንኳ የጎንደር አስተዳዳሪ ከነበሩት አስተዳዳሪዎችና ከንቲባዎች ስንቶቹ ቅማንት እንዳልነበሩ በድፍረት መናገር የሚችል የኮሚቴ አባል አለ? ታድያ ጎንደር ከተማን የቅማንት መናገሻ እንደርጋለንን ምን አመጣው? ጥድፊያው ገበሬውን ከእርሻ መሬቱ ላይ ለማፈናቀል ከተሜውንም “የአይንህ ቀለም አላማረንም” ከከተማችን ውጣ ለማለት ነው? የጎንደር ህዝብ አስተዳዳሪው አማራም ይሁን ቅማንት መከራውንም ደስታውንም እኩል ሲቀምስ ኑሯል። አሁንም እየኖረ ነው፤ ወደፊትም ይኖራል። ሰላሙን ለማደፍረስና ጎንደርን ለማዳማት በአክራሪ የኮሚቴ አባላት የሚሽረበውን ሴራ እንደእስከዛሬው ሁሉ ህዝቡ በአንድነት በመቆም ያከሽፈዋል።
ከጀርባ ያደፈጠው አካል የሚጠቀምበት የትግል ታክቲክ
አክራሪ የኮሚቴው አባላት አጀንዳቸውን ወደፊት ለመግፋት፣ ከአክራሪነታቸውም ባሻገር በመንግስት ተቀባይነት ለማግኘትና የሁከትና መለያየት ዓላማቸውን ለማሳካት የተለያዩ ዘዴዎችን ይጠቀማሉ።
  1. ህዝቡን መከፋፈልና ማሸማቀቅ፦ አክራሪዎቹ ቅማንትን ከቅማንት፤ ቅማንትን ከአማራ ይከፋፍላሉ። በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ መወያያቸው መድረክ ላይ አማራን ለመግለጽ የሚጠቀሙበት ቋንቋ በጣም አሳፋሪ ነው። ቅማንት መሆናቸው እስከሚያጠራጥር ድረስ። በአማራ ህዝብ ላይ ከፍተኛ የማጥላላት ስራ ያካሄዳሉ። ነፍጠኛ፣ ትምክህተኛ፣ ቆማጣ፣ ለማኝ፣ ድሃ፣ ፈሪ፣ የራሱ ታሪክ የለለው ወዘተ አማራው ላይ የሚለጥፉት ገለባ-አልባ ጭቃ ነው። እነዚህ ሰዎች የእነርሱ ተቃራኒ ከመሰላቸው የቅማንት ተወላጅም ቢሆን የጭቃ ጅራፋቸውን ማንሳታቸው አልቀረም። ከቅማንትነትም ወረድ ይሉና የጭልጋ ቅማንት፣ የጎንደር ዙሪያ ቅማንት፣ የአርማጭሆ ቅማንት፣ ግማሽ ቅማንት፣ ሩብ ቅማንት፣ 1/8ኛ ቅማንት ወዘተ በማለት ክፍፍሉን ያከፉታል። ከእነርሱ ጋር የሚስማማ ከሆነ 1/8ኛ ቅማንትም ቢሆን የእነርሱ ጀግና ነው፤ ባንፃሩ ደግሞ ሙሉ ቅማንት ሆኖ ከነሱ አስተሳሰብ ጋር ካልተስማማ ወይ ቅማንትነቱን ይሰርዙታል ወይም ባንዳ የሚል ታርጋ ይለጥፉበታል። በዚህ ሁኔታ ሰዎችን እያሸማቀቁ እነርሱ ወደ ሚፈልጉት ግን ለመሄድ ይሞክራሉ። ይህን ጉዳይ በማስረጃ እንመልከተው።
  2. አቶ በየነ አስማረ የተባሉ የብሄረሰቡ ተወላጅ ኢትዮጵያዊ ሲሆኑ የቅማንት የማንነትና ራስን የማስተዳዳር ጥያቄ የተነሳበትን አቅጣጫውን የመሳት ምልክቶች መታየት ሲጀምሩ ጉዳዩ ወደ ግጭት ከማምራቱ በፊት በተለያዩ ሚዲያዎች (ቪኦኤን ጨምሮ) ቀርበው የቀረበውን ጥያቄ በእርጋታ በመወያየትና በመደማመጥ መፍታት እንደሚያስፈልግ ተናገሩ። ሁሉንም ህዝብ ባሳተፈ ሰላማዊ መንገድ ችግሩ ካልተፈታ አላስፈላጊ የህዝብ ግጭት ሊያስከትል ይችላል በማለት ምክራቸውን አስቀድመው አቀረቡ። በኋላም እንደታየው ሰሚ በማጣታቸው አቶ በየነ አስቀድመው ያስጠነቀቁት መከራ ደረሰ። አቶ በየነ ሁሉም ነገር በሰላምና በአንድነት እንዲሆን በመመኘታቸው በአክራሪ የኮሚቴው አባላት ዘንድ በየማህበራዊ ሚዲያው ሁሉ የቅማንት ጠላት፣ ባንዳ፣ ከዚያም ወረድ አድርገው እርሱ “የጎንደር ዙርያ ቅማንት ስለሆነ ነው ይህን ያለው” ወዘተ በማለት ልያሽማቋቸው ሞክረዋል፤ አክራሪዎች ባይሳካላቸውም። እነአቶ በየነ አስማረ ግን ለሁለቱም ወንድማማች ህዝብ አንድነት ዛሬም በጽናት የሚቻላቸውን ሁሉ እያደረጉ ይገኛሉ።
  3. የአቶ ደሴ ግዛቱን ጉዳይ እንመልከት። አቶ ደሴ የአማራ ተወላጅ ኢትዮጵያዊ ሲሆኑ በጭልጋ ወረዳ አይከል ከተማ የሚገኘው ቬሩት የተሰኘ ዘመናዊ ሆቴል ባለቤት ናቸው። ይህን ሆቴል በመክፈታቸው ለከተማው ልማት አስተዋጽኦ አበርክተዋል፤ ለአካባቢው ነዋሪ ደግሞ የስራ እድል ፈጥረዋል። ይሁንና የአክራሪው ኮሚቴ አባላት አቶ ደሴን በፀረ-ቅማንትነት ፈርጀው በየማህበራዊ ድረ-ገጽ መወያያ መድረኮችና በቴሌኮንፈረሳቸው ከፍተኛ የሆነ የስም ማጥፋት ዘመቻ አካሄደውባቸዋል። ከመንግስት ጋር ለማናከስም የጎንደር ህብረትና የአርበኞች ግንቦት 7 አባል እንደሆኑ ቀስቅሰውባቸዋል። ከዚህም አልፎ ሆቴላቸው እንዲቃጠልና እርሳቸውም በተገኙበት እርምጃ እንዲወሰድባቸው አክራሪዎቹ ለተከታዮቻቸው በፌስቡክ ትእዛዝ አስተላልፈዋል። ይህም የአክራሪ ኮሚቴዎች ሁሉቱን ህዝብ የመከፋፈልና እርስ በእርስ የማጫረስ ቅስቀሳቸው አስረጅ ነው።
  4. ከወረዳ እስከ ፌደራል መንግስት ድረስ በየደረጃው የሚገኙ የመንግስት ተቋማትንና ኃላፊዎችን ለመከፋፈል ያላሰለሰ ሙከራ ማድረግ፦ መጀመሪያ ላይ የቅማንት ጥያቄን በማፈን የክልሉ መንግስት ውሳኔ እንዳይሰጥ የሚያደርጉ በሰሜን ጎንደር አስተዳደር ሊቀመንበርና ምክትላቸው የሚመራው የበለሳና የአለፋ ወረዳወች ቡድን ነው በማለት የዞኑን አስተዳደር ለመከፋፈል ሙከራ አደረጉ። ትንሽ ቆይተው ደግሞ ጋይንቴዎችና ፋርጦች ዋነኛ የቅማንት ጠላቶች ናቸው የሚል ቅስቀሳ ጀመሩ። በዚህ ወቅት ዋነኛ ጠላቶቻችን ናቸው የተባሉት አቶ ግዛት አቡየና አቶ አማረ ሰጤ ነበሩ።ይህ ሁሉ ሲሆን የክልሉን መንግስት የእነርሱ ደጋፊ አድርገው ይቀሰቅሱ ነበር። ከላይ እንደተገለጸው የክልሉ ም/ቤት ሐምሌ 2007 ዓ.ም ላይ ለቀረበለት የማንነትና የራስ አስተዳደር ጥያቄ አወንታዊ ምላሽ ሰጠ። በዚህ ጊዜ አክራሪዎቹ የጥያቄው መመለስ ሊያስደስታቸው ሲገባ እነርሱ ግን የክልሉ ም/ቤትን በጠላትነት ፈረጁ። በክልሉ መንግስት ከፍተኛ የአመራር አባላት ላይም ከፍተኛ የማጥላላት ዘመቻ በማህበራዊ ሚዲያው ማካሄድ ጀመሩ። አቶ ገዱ አንዳርጋቸው፣ አቶ አለምነው መኮንን፣ አቶ ደሴ አሰሜ፣ አቶ አገኘሁ ተሻገርና አቶ ያለው አባተ በአክራሪዎች የማጥላላት ዘመቻ ከተደረገባቸው የክልል አመራሮች ዋናዎቹ ነበሩ። እንደ ዞኑ አስተዳደር ሁሉ የክልሉን መንግስትና አመራሩን በጥላትነት ከፈረጁ በኋላ “የአፄዎች ናፋቂ” የሆነው የአማራ ክልል አመራር ችግራችን ሊፈታው ስላልቻለ ጥያቄያቸውን ለፌደሬሽን ም/ቤት ማቅረባቸውን አወጁ። የፌደሬሽን ም/ቤትም የቀረበለትን ጥያቄ ከመረመረ በኋላ የአማራ ክልል ም/ቤት ያስተላለፈውን ውሳኔ አጸደቀ። አክራሪ የኮሚቴው አባላት ግን እውነታውን ወደጎን በመተው የፌደሬሽንና የክልሉ ም/ቤቶች በቅማንት ጥያቄ አፈታት ላይ የተለያዩ በማስመሰል የክልሉ መንግስት ውሳኔውን እንዲቀይር በፌደሬሽን ም/ቤት ታዟል በማለት ህዝቡን የማደናገር እርምጃቸውን ቀጠሉበት። ቅስቀሳቸውንም ተከትሎ ከፍተኛ ደም መፋሰስና ንብረት መውደም ደረሰ። ከዚያ ሁሉ እልቂትና ውድመት በኋላም አክራሪዎች የፈደራሉ መንግስት ይደግፈናል የክልሉ መንግስት ግን ጥላታችን ነው የሚለውን የመከፋፈል ቅስቀሳ አላቆሙም። ለዚህም ይመስላል በቅርቡ በአቶ ካሳ ተክለብርሐን (የቀድሞው የፌደሬሽን ም/ቤት አፈጉባኤና የወቅቱ የፌደራል ጉዳዮች ሚንስትር) የተመራ ልኡክ ጎንደር ከተማ ከህዝቡ ጋር ባደረጉት ስብሰባ ላይ በቅማንት ጥያቄ አፈታት ላይ የፌደራል መንግስቱ ከአማራ ክልል መንግስት የተለየ አቋም እንደሌለው ለህዝቡ በይፋ የገለጹት። አቶ ካሳ በስብሰባው ወቅት 42 ቀበሌዎችን ያካተተ የቅማንት ብሄረሰብ የልዩ ወረዳ ም/ቤት እንዲቋቋምና የሚቀሩ ቀበሌዎች አሉ ከተባለም ወደፊት በጥናት እየተረጋገጠ የሚስተካከልበት አግባብ እንደሚኖር በማስገንዘብ የአክራሪ ኮሚቴዎችን በቅማንት ጥያቄ አፈታት የፌደራሉና የክልሉ መንግስት አልተስማሙም የሚለውን አፍራሽና ከፋፋይ ቅስቀሳ በተግባር ሰባብረውታል።
ይሁንና አክራሪ የኮሚቴው አባላት ህዝቡን የማጋጨትና የማተራመስ ቅስቀሳቸውን አሁንም ቀጥለውበታል።
ከጥያቄው ጀርባ በሰሜን አሜሪካ የሚገኙ አስተባባሪዎች
አክራሪ የኮሚቴው አባላትን በፕሮፓጋንዳ፣ ፋይናንስና ሎጀስቲክስ የሚያደሯጃቸውና የሚያሰማሯቸው ለራሳቸው የግል ጥቅም መሰረት ለመጣል የሚሯሯጡ በውጭ የሚኖሩ ግለሰቦችም ይገኙበታል። የእነዚህን ሰዎች ማንነትና የሰሩትንም ስራ ማየቱ ለብዙሃኑ አስተማሪ ስለሚሆን ለዛሬ ሦስቱን “የቅማንት ተቆርቋሪዎች” ነን ባዮች ዶሴ እንደሚከተለው እናቀርባለን።
  1. አቶ ጥጋቡ ክብረት ተቀባ፦ ይህ ግለሰብ የተወለደው ጎንደር ክ/ሀገር ጭልጋ ወረዳ ጮንጮቅ ቀበሌ ነው። ወደ 40 ዓመት አካባቢ አሜርካን አገር በሲያትል ዋሽንግተን ነዋሪ ነው። አቶ ጥጋቡ በደርግ ጊዜ ለአይከል ከተማ የኤሌክትሪክ ሀይል መብራት ለማስገባት በሚል ሽፋን ከሌላው የጭልጋ ተወላጅ አቶ እጹብ አሰፋ ገላጋይ ጋር በመተባበር ከአካባቢው ተወላጆች፣ ከሌሎች ኢትዮጵያውያንና አሜርካውያንም ጭምር ከ120ሺ እስከ 140ሺ ዶላር የሚገመት ገንዘብ ካሰባሰቡ በኋላ ገንዘቡን ተከፋፍለው ለግል መጠቀሚያ ካደረጉት ሰዎች ውስጥ ዋነኛው ነው። ከዚህ በተጨማሪም አቶ ጥጋቡ አቶ ደሳለኝ አደመ ከተባለ ግለሰብ ጋር በመሆን በፈረንጅ አቆጣጠር መጋቢት 12 ቀን 2002 ዓ.ም በሚኖርበት ሲያትል ዋሽንግተን የቅማንት ታሪካዊ ህብረተሰብ (Qemant Historical Society) የሚባል ድርጅት በስቴቱ አስመዝግቦ ነበር። በዚህ ድርጅት ስም ከመንግስት የበጀት መደጎሚያ 30ሺ ዶላር በየዓመቱ እየወሰደ አቶ ጥጋቡ ለግል መጠቀሚያ አድርጎታል። በ6ኛው ዓመት የዋሽንግተን መንግስት የአቶ ጥጋቡ ድርጅት የሚወስደውን የበጀት መደጎሚያ ለቅማንት ታሪካዊ ማህበረሰብ በሚገባ አለማዋሉን በኦዲት ስላረጋገጠ የአቶ ጥጋቡን ድርጅት በፈረንጅ አቆጣጠር ሐምሌ 1 ቀን 2008 ዓ.ም ጀምሮ ከድርጅትነት ተሰርዟል። በዚህም ምክንያት እስከዛሬ ድረስ በአሜርካ በሚኖሩ የአካባቢው ተወላጆች ከማህበራዊ ህይዎት የተገለለ ስው ነው። አቶ ጥጋቡ በቅማንት ጥያቄ ሽፋን በጎንደር የተፈጠረውን ሁከትና ደምመፋሰስ ከጀርባ ሆኖ በማቀድ፣ በማደራጀትና በመምራት ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል። ለዚህም በየቀኑ በስልክ፣ በኢሜል እንዲሁም በፊስቡክ በመገናኘት የተፈጠረውን ደምመፋሰስ ያስተባበረ ነው። አሁንም በዚህ አፍራሽ ተግባሩ እንደቀጠለ ይገኛል።
  2. አቶ ታደለ አሰፋ ገላጋይ፦ የተወለደው በጎንደር ክ/ሀገር ጭልጋ ወረዳ አይከል ከተማ ሲሆን አሁን የሚኖረው አሜርካን አገር በፖርትላንድ ኦሪገን ነው። አቶ ታደለ ከላይ በተራ ቁጥር 1 የተገለጸው የአቶ እጹብ ወንድም ሲሆን ለጭልጋ ወረዳ አይከል 2ኛ ደረጃ መሰናዶ ት/ቤት ማሳደሻ፣ የሽንት ቤት መስሪያ፣ ላቦራቶሪና ቤተ-መጽሐፍት ማቋቋሚያ የሚሆን በማለት ከአካባቢው ተወላጆችና ከሌሎችም ኢትዮጵያውያን የተሰበሰበውን 65ሺ ዶላር ወስዶ አዲስ አበባ ላይ የግል መኖሪያ ቪላ የሰራ ሰው ነው። አቶ ታደለ የአሜርካውን አስተባባሪ ኮሚቴ በመወከል በየጊዜው አዲስ አበባ በመሄድ እነአቶ ከፋለ ማሞን ከጭልጋ አዲስ አበባ አስመጥቶ አሜርካ በቴሌኮንፈረስ ያሰባሰበውን ገንዘብና የብጥብጥ አጀንዳ ሰጥቶ ይመለሳል። አቶ ታደለ በተለያዩ የፌስቡክ አካውንቶች በመጠቀም በአማራ ህዝብ ላይ የዘር ፍጅት ቅስቀሳ ያደረገ ነው። በጎንደር ግጭት በተካሄደባቸው ቦታዎች በሙሉ በተለይ ደግሞ በአይከል፣ በመተማና በማውራ ለተካሄደው ፍጅት ህዝቡን ለእልቂት እንዲነሳሳ ቀስቅሷል። በፎቶው እንደሚታየው አሮጊቶችና ሴቶችን ሳይቀር መሳሪያ እያስያዙ ለጦርነትና ለግድያ እንዲወጡ አስተባብሯል።
  3. ወ/ሮ አበባ ተፈሪ ንጉሴ፦ የተወለደችው ጎንደር ከተማ ነው። ላለፉት 35 ዓመታት አካባቢ ነዋሪነቷ አሜርካን አገር በሲያትል ዋሽንግተን ነው። ወ/ሮ አበባ ለሦስት ጊዜ በቁርባን አግብታ የፈታች ስትሆን አራትኛ ባሏ ይሆናል ተብሎ የነበረው “ጓደኛዋ” በሰላም አብረው አምሽተው ከእርሷ መኖሪያ ቤት ፊት ለፊት በመኪናው ውስጥ “በድንገት” ሞቶ በመገኘቱ በሲያትል የኢትዮጵያውያን ማህበረሰብ መነጋገሪያ ሆኖ ቆይቷል። ወ/ሮ አበባ በማህበራዊ ሚድያ ፀረ-አማራና ጥላቻ የተሞላበት ቅስቀሳ በየቀኑ ታራምዳለች። ለዚህም የፊስቡክ ገጿ ምስክር ነው። ከዚህ በፊት ከሌሎች የቅማንት ብሄረሰብ ተወላጅ ወንድሞች ጋር ለውይይት በቪኦኤ ቀርባ ሰላምና የቆየው አንድነታችን ይሻላል ያሉትን ወንድሞች (አቶ በየነ አስማረና አቶ አበበ ንጋቱን) በባንዳነት የከሰሰች የሁከት እናት ናት። በሰሜን አሜርካ የሚገኙትን የብጥብጥና መለያየት ደጋፊዎች ለማሰባበስ ከአቶ ጥጋቡና ከአቶ ታደለ ጋር በመተባበር በየሳምንቱ ቴሌኮንፈረስ ታስተባብራለች፤ ትመራለች። ለአገር ቤቱ አክራሪ የኮሚቴ አባላትም ገንዘብ እያሰባሰበች ትልካለች።
እንደ መደምደሚያ
ከላይ እንደተገለጸው እነዚህ ግለሰቦች ከ35 እስከ 40 ዓመታት በአሜርካ ሲኖሩ ለተወለዱበት አካባቢ ያበረከቱት አንዳች መልካም ነገር የለም። እንዲያውም ለመብራት ማስገቢያ፣ ለት/ቤት ማሳደሻ፣ ለላቦራቶሪና ለቤተመጽሐፍት ማቋቋሚያ ወዘተ እያሉ በአገሩና በህዝቡ ስም የሰበሰቡትን ወደ 200ሺ ዶላር የሚደርስ ገንዘብ ተከፋፍለው ለግል መጠቀሚያ አድርገዋል። ለራሳቸው የሚያከራዩት ቪላ ቤት አዲስ አበባ ላይ ሲሰሩ ተወልደው ላደጉበትና እንቆረቆርለታል ለሚሉት ለቅማንት ህዝብ ግን በስሙ ከመነገድ በስተቀር ያደረጉለት አንዳች ነገር የለም። ይባስ ብለው ለአካባቢው ልማት ከፍተኛ መዋእለ ንዋይ ያፈሰሱትንና ለወጣቱ የስራ እድል የፈጠሩትን እንደነ አቶ ደሴ ግዛቱ አይነት ሰዎች ባልዋሉበት እየወነጀሉ በፌስቡክ ስማቸውን በማጥፋት ለማሸማቀቅ ሙከራ ያደርጋሉ። ይህ ድርጊታቸው እነዚህ ግለሰቦች ከራሳቸው ፍላጎት ውጭ ለአካባቢ ልማትም ሆነ ለህዝቡ ምንም ደንታ እንደሌላቸው ያሳያል።
በአጠቃላይ እነዚህ ግለሰቦች አገር ቤት በቅማንት ስም እራሱን የሰየመውን አክራሪ የኮሚቴ አባላትን በመጠቀም ባጠቃላይ በጎንደር በተለይ ደግሞ በመተማ፣ በጭልጋና አርማጭሆ በየጊዜው የተከሰተውን ፀረ-ሳላም እንቅስቃሴ በጋራ አቅደዋል፤ አስተባብረዋል፤ መርተዋል። አክራሪ የኮሚቴው አባላትን በገንዘብ በመደለልና በተቃውሞ እንቅስቃሴ መሳተፋቸው ወደ ውጭ አገር ለመሄድ እንደሚረዳ በማማለል አካባቢው እንዲተራመስና ህዝቡ እንዲከፋፈል አድርገዋል። የሰላም ወዳድ ኢትዮጵያውያንን (አማራም ቅማንትም) መልካም ስም ለማጉደፍ ጥረዋል፤ ሰዎች እንዲገደሉ በፊስቡክ ትእዛዝ አስተላልፈዋል፤ ከፍተኛ ቅስቀሳም አድርገዋል። አሁንም ከአፍራሽ ተግባራቸው አልተቆጠቡም። በመሆኑም የእነዚህ ግለሰቦችንና ተላላኪያቸው የሆኑትን አክራሪ ትቂት የኮሚቴ አባላትን ማንነትና እኩይ ዓላማ በአግባቡ በመረዳት ወንድማማች የሆነው የአማራና ቅማንት ህዝብ በጋራ ቆሞ የጋራ ባህሉንና አገሩን ሊጠብቅ ይገባዋል። ለዚህ አጋዥ ይሆን ዘንድ ሌሎች የችግሩ ፈጣሪ የሆኑ ግለሰቦችንም በየደረጃው ያለው ህዝብ እንዲያውቃቸው በተከታታይ ማንነትቸውንና ህዝቡን ለመበታተን የሚያደርጉትን ድርጊት በመረጃ እየተደገፈ በተከታታይ መቅረቡ ይቀጥላል። እስከዚያው ቸር እንሰንብት።
Alemu.yigletie@gmail.com

No comments:

Post a Comment

wanted officials