Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, July 25, 2016

“ግማሹ መሬቱን… ሌላው ማንነቱን በወያኔ ሲነጠቅ!!” – ከአውስትራሊያ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ማኅበራት ም/ቤት የተሰጠ መግለጫ


australia ethiopians
በኢማማምአ የተሰጠ መግለጫ!!
እ.ኤ.አ 21/07/2016
በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ እነ ከተማ ይፍሩና እውቁ ደራሲ አዲስ ዓለማየሁ ከዚያ ዘመን ትውልድ ራሳቸውን እጅግ በጣም ተራማጆች አድርገው ይቆጥሩ ስለነበር በወቅቱ በምሥራቁ አውሮፓ የተራማጅነት ምልክት ተደርጋ የምትቆጠረውን ቀይ
ባጅ (ምልክት) በእግራ የደረት ኪሳቸው ላይ ይሰኩ እንደነበር የዚያ ትውልድ መጻጽፎች በዋቢነት የሚጠቀሱ ሲሆን እንዲሁም በዓለማችን የተለያዩ ጠንፍ ላይ የሚገኙት እነ ቸጉቤራና ሆቺሚን የኢትዮጵያን የአምስት ዓመት የአርበኝነት የነፃነት የሽምቅ ውጊያ ስልትን ለነፃነት ትግላቸው በያሉበት በዋቢነት መጠቀሙ እንዳለ ሆኖ የቸጉቤራ ለሰው ልጆች እኩልነት ሲል (በወቅቱ በነበረው የፖለቲካ ቅኝት ለማለት ነው) የወጣ የወረደባቸው ጋራ ቁልቁለቶችና የዘመራቸው የእኩልነት መዝሙሮች እንደ ሰደድ እሳት በአዲሱ ትውልድ ሕሊና ውስጥ በመቀጣጠላቸው በሂደት በ1960ቹ አጋማሽ አካባቢ በነ አዲስ ዓለማየሁ እግር የተተካው ኢትዮጵያዊው ወጣቱ ምሁርና በተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች እጅግ በጣም ቀልብ የሚስቡ
ብሔራዊ መፈክሮችን አንግበው ለአብነት ያህል “መሬት ላራሹ፣ ሕብረተሰባዊነትና እኩልነት፣ ሕዝባዊ መንግሥት፣ ወ.ዘ.ተ” የመሳሰሉትን በግልጽና በድፍረት በአደባባይ ያስተጋቡ ነበር::


No comments:

Post a Comment

wanted officials