Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Saturday, July 23, 2016

የጎንደር ዜናና ብአዴን – ግርማ ካሳ

13669846_228558014204928_6547288386076616196_nዛሬ ሐምሌ 17 ቀን 2008 ዓ.ም. ጎንደር ላይ ሲካሄድ ታስቦ የነበረው ሰላማዊ ሰልፍ ወደሚቀጥለው ሳምንት ማለት ወደ ሐምሌ 25 ቀን 2008 ዓ.ም እንደተዘዋወረ መረጃዎች እየወጡ ነው። ከጥቂት ቀናት በፊት የአገር ሽማግሌዎች ከክልሉ አስተዳደር ጋር ባደረጉት ዉይይት፣ አስተዳደሩ ለ10 ቀን ሰልፉ እንዲራዘም መጠየቃቸው ይታወሳል።
ለሰላም ሲባል የክልሉ አስተዳደር ጥያቄን በማክበር እና በጎንደር ዙሪያና በሌሎች የአገራችን አካባቢዎች የሚኖሩ ወደ ጎንደር ከተማ እንዲመጡ ሁኔታዎችንም ለማመቻቸት ሲባል እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።
በተያያዘ ዜና በብአዴን ዉስጥ ከፍተኛ የሆነ መከፋፈል እንዳለም ይነገራል። ታማኝ ምንጮዎቸ በመግለጽ አንድ ታዋቂ የፖለቲክ አክቲቪስት እንደ ጦምረው ብኢዲን ክሦስት ተክፍሏል ።
የመጀመሪያው ክፍል የክልሉ አስተዳዳሪ የሆኑት እነ ገዱ አንዳርጋቸው ያሉብት፣ አብዛኛው የብአዴን አባላት የደገፉት፣ “የአማራ ው ህዝብ ተወካዮች እስክሆን ድረስ የሕህት የበላይነት ይብቃ” የሚል አለመካከት ያላቸው ሲሆን፣ ይህ ቡድን ክፍተኛ የህዝብ ደጋፍ ያለው ቡድን ነው። አቶ ገዱን ጨምሮ፣ የተወሰኑ የፖሊት ቢሮ አባላት ያሉበት ሲሆን፣ ከግማሽ በላይ የሆኑ የማክላዊ ኮሚቴ አባላትን ያካተተ ነው። መካክለኛው እና ዝቅተኛ የሆኑ የብአዴን አመራሮችና አባላት በብዛት ማለት ይቻላል የሚደገፉት ቡድን ነው። ከአንድ አመት በፊት በባህር ዳር ብአዴን ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ ” እነርሱ ባለ ፎቅ እና ሎተሪ ሻጭ” በሚል የጉባኤው አባላት በሕወሃት ላይ እየደጋገሙ ምሬታቸውን ሲገልጹ እንደነበረም የሚታወስ ነው።
ሁለተኛው ቡድን እነ ብናልፍ አንዱለምን ያካተተ የመሀል ስፋሪ ቡድን ነው። የተወስኑ ስዎችን የያዘ ስልጣን ናፋቂ ቡድን፣ ግን በሚደረገው የዉስጥ ትግል አሽናፊው ማን እንደሆነ እየተጠባብቀ ያለ ቡድን።
ሶስተኛው በአለምነህ መኮነን፣ ደመቀ መኮንን …ያሉበት የወያኔ አሽክርነት የሚደግፉ ነባር አመራሮች ያካተተው ቡድን ነው። ይህ ቡድን በሕወሃት አዝማችነትና ትእዛዝ የሚንቀሳቀስ እንደሆነ ይነገርለታል።
አቶ ደምቀ ተቀዳሚ ም/ጠሚኒስቴር ሲሆኑ በአሁኑ ወቅት የየአማራው ክልል ከፍተኛ ትንቅንቅ ከሕወሃት ጋር እያደረገ ባለበት ወቅት፣ ህወሃቶች በሚቆጣጠሩት ሜዲያ ህዝቡ እያስፈራሩና እየሰደቡ ባለበት ወቅት ዝምታን የመረጡ ደካማ አመራር ናቸው።
አቶ አለምነህ መኮንን ከፍተኛ የሕወሃት ጥበቃ የሚደረግላቸው የክልል /ፕሬዘዳንት የሆኑ ሰው ናቸው። የአማራውን ክልል ህዝብ ” ምንም ሳይኖረው የሚመጻደቅ፣ በእግሩ የሚሄድ ልፋጫም የሆነ” በማለት መሳደባቸው፣ ያንንም ተከትሎ ድፍን የባህር ዳር ሕዝብ ወጥቶ ሰዉዬዉን ማወገዙ ይታወቃል። ሆኖም የሕወሃት ጋሻ ጃግሬ በመሆናቸው ያን ያህል በሕዝብ የተጠሉ ሰዉዬውም ቢሆኑም፣ አሁንም በስልጣናቸው ላይ ናቸው። ህወሃቶች በተለያዩ ጊዜ ግምገማ እያሉ አቶ ገዱን በማንሳት አቶ አለመንሀን የክልሉ አስተዳዳሪ ለማድረግ ብዙ የሞከሩ ቢሆንም እስከአሁን ግን ሳይሳካላቸው ቀርቷል።
ይህ በብአዴን ዉስጥ የሚደረገው የዉስጣዊ ትግል በሕዝቡና በሕወሃት መካከል የሚደረግ የተዘዋዋሪ ትግል ነው። (proxy) የህዝብ ድጋፍ ያለው የነገዱ አንዳርጋቸው ቡድን ወይስ የህወሃቱ አሽከር የነ አለምነህ መኮንን ቡድን አይሎ ይወጣል?? ወሳኙ ሕዝብ ነው።
ህዝብ እንቅሳሴዉን አጠናክሮ ከቀጠለ የሕወሃት ተጽኖና ሃይል ካነሰ የተሻለ ዉጤት ይመጣል። ግን ህዝብ ከተዘናጋ፣ ህወሃት በዘዴና በጥበበ እያሰራ፣ እየገደለ በገንዘብ እየደለለ ህዝብን መከፋፈል ከቻለ ግን የሕወሃት የግፋ አገዛዝ በባሰ ሁኔታ ይቀጥላል።
ሊሰመርበት የሚገባ ተቃዉሞው ከጎንደር ዌወደ ጀግናው የባህር ዳር፣ የደንረ ብርሃኑ፣ የደብረ ማርቆስ፣ የወሎ…ህዝብ መሸጋገር አለበት።

No comments:

Post a Comment

wanted officials