Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Friday, July 29, 2016

የቃሊቲ እስርቤት ታሳሪዎች ለ ፌደራል ማረሚያ ቤቶች ዳይረክተር የላኩት ግልፅ ደብዳቤ ‪



የቃሊት እስርቤት ታሳሪዎች ለ ፌደራል ማረሚያ ቤቶች ዳይረክተር የላኩት ግልፅ ደብዳቤ
ለፌደራል ማረሚያ ቤቶች ዳይረክተር


በፌደራል ማረሚያ አስተዳደር ካሉ ማረሚያ ቤቶች አንዱ የቃሊቲ ማረሚያ ቤት ሲሆን በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ውስጥ የሚሰሩት መጥፎ ድርጊቶች ወይንም የመልካም አስተዳደር ችግር ለሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እና ለሚመለከታቸው የመንግስት ተወካዬች ተነግሮ ዋና አስተዳደሪ ከተቀየረ በኃላ የተወሰኑ ለውጦችን መመልከታችን የማይካድ ቢሆንም ነገር ግን የቀድሞ አስተዳደር አመለካከት እና ህገወጥ አሰራሮች አንዳንዴ በታራሚው ላይ በመጫን የቀድሞውን አስተዳዳሪ በደሎች ለመድገበ እና በዚህ ማሃል በሚፈጠሩት ግር ግር ማጥቃት የሚፈልጉትን ታራሚዎች አጥቅቶ የግል ጥቅማቸውን በማሳደድ መንገድ እየጠረጉ ያሉትን አባላት ለመቆጣጠር የሚቻል የሚመስሉ ምልክቶች እየታዩ ነው፡፡

የዚህ ችግር መሰረት ባለፈው አመታት ለመልካም አስተዳደር እጦት
ዋናው ተዋናይ የነበሩት አባላት አሁንም በሀላፊነት ላይ መሆናቸው ነው። የዋናው አስተዳዳሪው ጥረት ብቻውን መሰረታዊ ለውጥ ሊያመጣ አይችልም፡፡ እነዚህ ሀላፊዎች የሲጋራና የሀሺሺ ነጋዴዎች ተላላኪዎች በመሆናቸው እና ይህን የጥቅም መረባቸውን ዘርግተው የሚነግዱበት ሲሆን በአሁን ሠዐት በማረሚያ ቤቱ ውስጥ አንድ ፍሬ ሲጋራ 25 ብር አንድ ፓኬት 500 ብረ አንድ እሰቴክ 5000 ብር እየተሸጠ በመሆኑ መንግስት እንዲያርሙ የተሰጣቸውን ሃላፊነት ጥለው የግል ጥቅማቸውን እያሳደዱ ይገኛሉ።

በማረሚያ ቤት ውስጥ የግል ጥቅማቸውን ለማስከበር የሚራራጡ ባለስልጣኖች ዛሬም በስብሰባ ያጋለጣቸውን ታራሚዎች ስም በማጥፋት አደገኛ ነው ያመልጣል ወይም ከተቃዋሚዎች ጋር ይገናኛል ይነጋገራል ወዘተ በሚል ማረሚያ ቤቱ በስጋት እንዲያያቸው በማድረግ እነዚህን ታራሚዎች የማሸማቀቅ ዘመቻ ቀጥለዋል።

የቃሊቲ ማረሚያ ቤት የጥበቃ እና የደህንነት ሃላፊ ሱፐር እንዲፔንደንት ተስፈሚካኤል እጃቸው እየተጠመዘዙ የቀድሞው የጥበቃ ሃላፊ ኢንድፔንደንት ሀጎስ የሰራቸውን ስህተቶች እየደገመው ነው ።ለምሳሌ የቀድሞ የጥበቃ የደህንነት ሀላፊ የነበሩት ሱፐር ኢንድፔንደት ሀጎስ ወዳጅ ነህ ያዙዋቸው የነበሩት የስራ ሃላፊዎች ታራሚዎችን ዛሬም ዝዋይ ለቅጣት መላክ፣ ጨለማ ቤት ማጎር ፣ማስፈራራትና መዛት ቀጥለዋል።

በ29/ 8 / 2008 ወደ ዝዋይ የተጫኑ እና አሁንም ዝዋይ ጨለማ ቤት የሚገኙ ታራሚዎች የተመረጡት በሱፐር እንዲፔንደት ተስፋ ሚካኤል አሰግድ እና በዞን 4የቀድሞው ዞን አንድ ዞን ተጠሪ ገብረ ማሪያም የተመለመሉ ናቸው፡፡ ገብረማሪያም በዞን አንድ ውስጥ እልቂት ለመፍጠር ተግቶ የሚሰራ ሰው ነው ። ለምሳሌ 11/11/2008 ተስፋ የሚወጡ ማእከል የሚጠጡ ታራሚዎች ወደ ስራ ከሄዱም ቡሃላ ቤት የቀሩትን ታራሚዎች ሰብስበው ውጡ በማለት ሁሉንም ካስወጡ ቡሃላ 1ኛ ቤት 50 የሚደርሱ የፖሊስ አባላት እየመሩ አስገብተው የታራሚው ኮሚቴ ወይም ታራሚው በሌለበት ፍተሻ በማድረግ ከተለያዩ ታራሚዎች ከ15ሺ ብር በላይ አዘርፈዋል፡፡ ከዛም አልፎ ገንዘብ ጠፍቶናል ብለው የጠየቁትን ታራሚዎች ጊቢው ላይ አድማ ወይም ረብሻ ልታስነሱ ነው በማለት አስፈራርተዋል፡፡ ሌላው በዚህ ፍተሻ ታራሚዎች የሚተኙበት ምንጣፎች፣ ፎጣዎች፣ አንሶላዎች፣ መቀመጫ ወንበሮች፣ የውሃ መጠጫ ትናንሽ ጀሪካኖች ሁሉ ተወስደዋል፡፡ በጣም የሚገርመው ነገር ደግሞ የዞን ተጠሪው ገብረማሪያም ሁለት ቤት በማስገንባት አንድ ቤት የእሱ ጠላቶች መሰብሰቢያ አንዱ ቤት ደግሞ የሱ ወዳጆች መስብሰቢያ ማድረግ ከጀመረ የሰነበተ ሲሆን በዚህ ፍተሻ ቀን ፖሊሶች አንደኛ ቤት ፈትሸው ሁለተኛ ቤት እንደጀመሩ እዚኛው ቤት እነታምራት ገለታን የመሳሰሉ ትልልቅ ሰዎች ያሉበት ቦታ ነው በማለት ለፍተሻ የገቡትን ፖሊሶች እንዲወጡ አድርጎዋል።

የዞን ተጠሪው ገብረ ማሪያም አላማው የነበረው በፍተሻው ጊዜ በተወሰደው ንብረት ምክኒያት ታራሚው ረብሻ እንዲያስነሳ እና በዚህ ግርግር ሊያስመታ የፈለገውን ለማስመታት ነበር፡፡ ይህ ያቀደው ሴራ አልሆንለት ሲል ደግሞ በ12 / 11 /08 የአንደኛ ቤት ታራሚዎች አልቆጠርም ብለው ስራ እንደወጡ በማድረግ በማታው ቆጠራ ከ20 በላይ የሚሆኑትን ፖሊሶች ዱላ አስይዘው አስገበቶ ነገር ለመቀስቀስ ሞክሮዋል፡፡ የዞን አንድ ተጠሪ ሻለቃ ገብረማሪያም የተሳሳቱ ኢንፎርሜሽኖች ለሃላፊዎች በመስጠት መስሪያ ቤቱን ለታራሚዎች መልካም ሀሳብ እንዳያደርግ ቀን እና ለሊት የሚሰራ ሰው ነው። ሻለቃ ገብረማሪያም በተለያየ ስብሰባዎች ላይ ታራሚው ሲጋራ ሀሺሽ የሚያስገባ መሆኑን ከ10 ሠዐት ቡሃላ ቢሮው ውስጥ ከነሱ ውጭ ማንንም እንደማያነጋግር እነዚህ ታራሚዎች ለሚሰሩት ማጭበርበር ስራ ቢሮ ውስጥ በስልክ በማገናኘት ከሚያጭበረብሩት ገንዘብ የጥቅም ተካፋይ መሆኑን በተለያዩ መንገዶች ለሀላፊዎች ቢደርስም የተሰጠ ውሳኔ የለም፡፡

ይህ ሳያንሰው ጊቢ ውስጥ ማንኛውም ችግር ቢነሳ ተጠያቂዎች ናቸው የሚል ፊርማ ሆነ ማህተም የሌለው የታራሚዎች የስም ዝርዝር በቦርድ ላይ አውጥቷል። ይህ ሰው እርስ በርሳችን ሳያጨራርሰን ካልተነሳልን ለሚፈጠረው ችግር ተጠያቂ ማን ነው? ይንን በጥልቀት ያስቡበት እና ያለብንን ችግር በሃላፊነት በኢትዮጲያዊነት መንፈስ ይፍቱልን፡፡

ከሰላምታ ጋር

ግልባጭ

1 ለኢትዮጲያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን
2 ለቃሊቲ ክፍለ ከተማ ማረሚያ ቤት አስተዳደር
3 ለቃሊቲ ክፍለከተማ ማረሚያ ቤቶች ጥበቃና ደህንነት ሀላፊ
4 ለኢትዮጲያ ህዝብ በሶሻል ሚዲያ

No comments:

Post a Comment

wanted officials